AbiyAhmed

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለዶናልድ ትራምፕ እነኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለዶናልድ ትራምፕ እነኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ

የዓለማችን ልዕለ ሀያል ሀገር የሆነችው አሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እየተካሄደ ሲሆን የሪፐብሊካኑ ዶናልድ ትራምፕ እየመሩ ገኛሉ፡፡ ትራምፕ እስካሁን በተረጋገጡ የወኪል መራጮች ምርጫ አማካኝነት 267 በ224 ድምጽ እየመሩ ይገኛሉ፡፡ አስቀድሞ 270 የወኪል መራጮችን ድምጽ ያገኘ እጩ 47ኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ይሆናል በሚለው ህግ መሰረት ዶናልድ ትራምፕ በይፋ ማሸነፋቸውን ለማወጅ ሶስት ድምጽ ብቻ መቅረቱን ተከትሎ በርካታ የዓለማችን ሀገራት አስቀድመው እንኳን ደስ አለዎት መልዕክታቸውን እያስተላለፉ ናቸው፡፡ ከነዚህ መካከልም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) አንዱ ሲሆን ዶናልድ ትራምፕ ምርጫውን ስላሸነፉ እንኳን ደስ አለዎት፣ ወደ መሪነት እንኳን ድጋሚ መጡ አብረን እንደምንሰራ ተስፋ አደርጋለሁ ብለዋል፡፡ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በበኩላቸው ለዶናልድ ትራምፕ እና ባለቤታቸው እንኳን ወደ…
Read More
ኢትዮጵያ ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታት ከግብር ነጻ እድል ፈቀደች

ኢትዮጵያ ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታት ከግብር ነጻ እድል ፈቀደች

የኢትዮጵያ ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች አውደ ርዕይ በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በአውደ ርዕዩ መክፈቻ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ለጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች ወይም ስታርት አፕ የተለያዩ ማበረታቻዎችን መደረጉን ተናግረዋል፡፡ ለስራ ፈጣሪዎች ከተደረጉት ማሻሻያዎች መካከል ከግብር ነጻ እድል፣ ከውጭ ንግዶች የሚያገኟቸውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ሙሉ ለሙሉ እንዲወስዱ፣ ንግድ ፈቃድ ለማውጣት የግድ ቢሮ ያስፈልግ የነበረውን ማንሳት፣ አዲ ሀሳብ ላላቸው ብድር ማመቻቸት እና ሌሎችም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ይህ አውደ ርዕይ ለ20 ቀናት ይቆያል የተባለ ሲሆን ጎብኚዎች ወደ ሳይንስ ሙዚየም በማቅናት መግባት እና መጎብኘት እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡ ከተደረጉ ማሻሻያዎች መካከል አንዱ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች ሃሳባቸውን ወደ ተግባር ለማዋል በሚፈልጉበት ወቅት…
Read More
እየሰጡ መንሳት

እየሰጡ መንሳት

በበፍቃዱ ኃይሉ ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያን ጠቅላይ ሚኒስትርነት ከኃይለማርያም ደሳለኝ ከተረከቡ ስድስት ዓመታት ተቆጠሩ። ዐቢይ በእነዚህ ዓመታት የተከተሉት የአመራር ሥልት በፍቃዱ ኃይሉ “እየሰጡ መንሳት” የሚለው አባባል ይገልጸዋል የሚል አተያይ አለው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያን የሥልጣን ማማ ከተቆናጠጡ እነሆ ዛሬ መጋቢት 24፣ 2016 ስድስት ዓመት ሞላቸው። በዘመናዊ ፖለቲካ ከአንድ የአገር መሪ የሚጠበቁት መሠረታዊ ኃላፊነቶች ሰላም እና መረጋጋት ማስፈን፣ ሕግ እና ስርዓት ማበጀት እንዲሁም ሥራ መፍጠር እና ኢኮኖሚ ማረጋጋት ናቸው። እነዚህ ዘርፎች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እምብዛም ናቸው። ይልቁንም በነውጥ እና ወጀብ እየተላጋች በምትሔደው መርከብ ውስጥ ወደ ካፒቴኑ መንበር ለመውጣት እርካቡ ላይ መንጠላጠል እንዲሁም መንበሩ ላይ ተደላድሎ መቀመጥ ግን ይችሉበታል። ይህንን…
Read More
የውጭ ሀገር ዜጎች ቤት እና መኪና መግዛት ሊፈቀድላቸው ነው ተባለ

የውጭ ሀገር ዜጎች ቤት እና መኪና መግዛት ሊፈቀድላቸው ነው ተባለ

የኢትዮ ቴሌኮም 10 በመቶ ድርሻም በሁለት ወራት ውስጥ መሸጥ እንደሚጀመር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ተናግረዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) “ታማኝ“ ግብር ከፋዮች ከተባሉ ነጋዴዎች ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል፡፡ እነዚህ “ታማኝ“ ግብር ከፋዮች የተባሉ ነጋዴዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ማብራሪያ እንዲሰጧቸው ጥያቄዎችን አቅርበዋል፡፡ ካቀረቧቸው ጥያቄዎች መካከልም የደህንነት ችግሮች፣ የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት እጥረት፣ የግብር እፎይታ ማነስ፣ የብድር አቅርቦት እጥረት፣ የማያሰሩ ፖሊሲዎች መብዛት እና የፖሊሲዎች በፍጥነት መቀያየር ችግሮች እንዲሁም መንግስት ለኢኮኖሚው ተገቢውን ትኩረት አለመስጠት የሚሉት ዋነኞቹ ናቸው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምላሻቸውም መንግስታቸው ባለፉት አምስት ዓመታት ኢኮኖሚውን ለማሻሻል የተደረጉ ጥረቶችን እና በቀጣይ የመንግስታቸው ትኩረቶች ዙሪያ አድርገዋል፡፡ ከተሰጡ ምላሾች መካከልም የግብር ጉዳይ አንዱ ሲሆን ኢትዮጵያ ኢኮኖሚው…
Read More
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በጸጥታ እና ዲፕሎማሲ ተቋማት ላይ የአመራር ሹም ሽር አደረጉ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በጸጥታ እና ዲፕሎማሲ ተቋማት ላይ የአመራር ሹም ሽር አደረጉ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አዳዲስ ሹመቶችን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበው አጸድቀዋል፡፡ በዚህም መሰረት የብሔራዊ ደህንነት ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ተመስገን ጥሩነህ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሲሆኑ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የቀድሞ አምባሳደር የነበሩት ታዬ አጽቀስላሴ ደግሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነዋል፡፡ እንዲሁም ዶክተር መቅደስ ዳባ ደግሞ ከጤና ሚኒስትርነት ሀላፊነታቸው የመልቀቂያ ደብዳቤ ላሰገቡት ዶክተር ሊያ ታደሰ ምትክ ሆነው ተሾመዋል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የደህንነት አማካሪ የነበሩት ሬድዋን ሁሴን ደግሞ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይረክተር ተሹመዋል። አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሆነው ከመስራታቸው በፊት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኢታ፣በኤርትራ እና አየርላንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው አገልግለዋል፡፡ ትዕግስት ሃሚድ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና…
Read More
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ሆነው ተሾሙ

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ሆነው ተሾሙ

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ሆነው ተሾሙ ጠቅላይ ሚኒስተር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የትምህርት ሚኒስትሩን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር አድርገው ሾሙ። ጠቅላይ ሚኒስተሩ ሹመቱን የሰጡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ሆኖ እንዲቋቋም በ1294/23 የራስ ገዝ አዋጅ በረቀቀው መሠረት እና የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሄደው 23ኛው መደበኛ ስብሰባ የዩኒቨርሲቲዎችን የራስ ገዝ ማቋቋሚያ ደንብ ላይ ተወያይቶ ማጽደቁን ተከትሎ ነው። በመሆኑም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ነጻነት እንዲረጋገጥ፣ ከፖለቲካዊም ሆነ አስተዳደራዊ ጣልቃ ገብነት ነጻ ሆነው የመማር ማስተማር እና የምርምር ሥራዎችን በላቀ መልኩ እንዲፈጽሙ እንዲሁም የሰው ሀብት እና የፋይናንስ አስተዳደር ነፃነትን በማረጋገጥ በሀገሪቱ የማኅበራዊ እና…
Read More
የተባበሩት አረብ ኢምሬት ፕሬዝዳንት ኢትዮጵያን ለመጎብኘት አዲስ አበባ ገቡ

የተባበሩት አረብ ኢምሬት ፕሬዝዳንት ኢትዮጵያን ለመጎብኘት አዲስ አበባ ገቡ

የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ፕሬዝዳንት ሼክ መሃመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል። ሼክ መሃመድ ቢን ዛይድ አል ናህንያን አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል። ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከተለያዩ የመንግስት የስራ ኃፊዎች ጋር ተገናኝተው እንደሚወያዩ ይጠበቃል። ሼክ መሃመድ ቢን ዛይድ ፕሬዝዳንት ከሆኑ በኋላ በኢትዮጵያ ጉብኝት ሲያደርጉ ይህ የመጀመሪያቸው ሲሆን ከዚህ ቀደም የአቡዳቢ አልጋ ወራሽ በነበሩበት ወቅት በ2018 በኢትዮጵያ ጉብኝት አድርገው ነበር። ሁለቱ ሀገራት የጠበቀ ወዳጅነት ያላቸው ሀገራት ሲሆኑ በተለይም በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ወደ ዱባይ እና አቡዳቢ በማምራት በመስራት ላይ ናቸው፡፡ እንዲሁም ሁለቱ ሀገራት በሰው ሀብት ልማት፣ በንግድ…
Read More
የአማራ ክልል የፌደራል መንግስት ጣልቃ እንዲገባ በይፋ ጠየቀ

የአማራ ክልል የፌደራል መንግስት ጣልቃ እንዲገባ በይፋ ጠየቀ

በአማራ ክልል ያጋጠመውን የፀጥታ መደፍረስ በመደበኛ የህግ ማስከበር ስርአት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ በመገኘቱ የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ እንዲተገብር የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጠየቀ። በክልሉ የተከሰተው የሰላም መደፍረስ ከፍተኛ ሰብአዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ እያደረሰ መሆኑን የክልሉ መንግስት አስታውቋል። የተከሰተውን የፀጥታ ችግር በቁጥጥር ስር ለማዋል እስካሁን በክልሉና በፌደራል የፀጥታ ሃይሎች በኩል በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸው ይታወቃል። ሆኖም በክልሉ ያለው የፀጥታ መደፍረስና ጥቃት በንፁሃን ዜጎች ላይ እያደረሰ ያለውን ጉዳት በአስቸኳይ ለማስቆም የፌደራል መንግስት ከመደበኛው የህግ ማስከበር ስርአት ባሻገር በኢፌዴሪ ህገ መንግስት መሰረት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ በአፋጣኝ እንዲተገበር ነው የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የጠየቀው። ክልሉ ወደ ቀደመ መረጋጋቱ እንዲመለስ ዜጎች ሰላማቸው ተመልሶ አርሶአደሩ…
Read More
ሰላምዊት ዳዊት የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሀላፊ ሆነው ተሾሙ

ሰላምዊት ዳዊት የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሀላፊ ሆነው ተሾሙ

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ሰላማዊት ዳዊትን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ሀላፊ አድርገው ሾሙ። የኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት ሶስት ከፍተኛ አመራሮች ከሀላፊነት መነሳታቸው ተገልጿል። ፓስፖርት እና መሰል የዜግነት አገልግሎቶችን ለመስጠት የተቋቋመው የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ተቋም ቅሬታዎች ሲቀርቡበት ቆይተዋል። ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ላለፉት አንድ ዓመት ከመንፈቅ የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎትን በዋና ዳይሬክተርነት ሲመሩ የነበሩት አቶ ብሩህተስፋ ሙልጌታን፣ በምክትል ዳይሬክተርነት ሲያገለግሉ የነበሩት ፍራኦል ጣፋ እና ታምሩ ግንበቶን ከኅላፊነት አንስተዋል። የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ህዝብ ግንኙነት እና ኮሙንኬሽን ሀላፊ ወይዘሮ ማስታዋል ገዳ ለአልዓይን እንዳሉት ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት ከሰኔ 12 ቀን 2015 ዓም ጀምሮ ተቋሙን በዋና ዳይሬክተርነት እንዲመሩ መሾማቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ደርሶናል ብለዋል። እንዲሁም…
Read More
ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞችን ተከለች

ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞችን ተከለች

ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞችን ተከለች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ "በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞች ተተክሏል" ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በዛሬው እለት 567 ሚሊዮን ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል። በአንድ ቀን 500ሺ ችግኝ የመትከል ዘመቻ አማካኝነት በሀገሪቱ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ችግኝ ሲተክሉ የሚያሳዩ ፎቶዎች እና ቪዲዮዎች ተለቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የችግኝ ተከላው" ለኢትዮጵያ ትልቅ ስኬት" ነው ሲሉ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በዚህ አመት ብቻ ከካርቦን ሽያጭ 52 ሚሊዮን ዶላር ማግኘቷን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የችግኝ ተከላው ስራ በዚሁ ከቀጠለ ከካርቦን ሽያጭ የምታገኘው ገቢ በእጥፍ እንደሚጨምር ገልጸዋል። ይሁንና በአንድ ጀምበር ተተከለ የተባለው የችግኝ መጠን በትክክል ስለመተከሉ በገለልታኛ አካል አልተረጋገጠም።
Read More