Diplomacy

ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ባሉ ዲፕሎማቶች ላይ የጉዞ ገደብ ጣለች

ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ባሉ ዲፕሎማቶች ላይ የጉዞ ገደብ ጣለች

መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ ዲፕሎማቶች ለመንግሥት ሳያሳውቁ ከከተማ እንዳይወጡ ደብዳቤ ተላከላቸው፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መቀመጫውቸን በአዲስ አበባ ላደረጉ ዲፕሎማቶች ለመንግሥት ሳያሳውቁ ከከተማ እንዳይወጡ ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡ ከአንድ ሳምንት በፊት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ የተላከው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው፣ ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ድርጅቶች በአገሪቱ ድንበር ውስጥ ለሚያደርጓቸው ማናቸው እንቅስቃሴዎች ቅድመ ፈቃድ እንዲጠይቁ አሳስቧል፡፡ በአዲስ አበባ ለሚገኙ ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ተቋማት፣ ዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ ድርጅቶችና መንግሥታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ ከአዲስ አበባ ውጭ የሚያደርጓቸውን ጉዞዎች በተመለከተ በሚኒስቴር መሥሪያ ቤት በተቀመጠ የቅድሚያ ማሳወቂያ ፎርም ከሞሉ በኋላ መሆን እንዳለበት አመላክቷል፡፡ ይሁን እንጂ ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ የተጻፈው ደብዳቤ ማስጠንቀቂያው ለሥራ ወይም ለግል ጉዳይ የሚጓዙትን እንደሆነ በግልጽ አያስረዳም ሲል…
Read More
ብናልፍ አንዱዓለም በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ተሾሙ

ብናልፍ አንዱዓለም በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ተሾሙ

የቀድሞው የሰላም ሚኒስትር የነበሩት አቶ ብናልፍ አንዱዓለም ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው መሾማቸውን የፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት አስታውቋል። በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩት ስለሺ በቀለ ባሳለፍነው ግንቦት ወር ላይ መልቀቂያ ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡ አምባሳደር ስለሺ በቀለ  በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደርነት ሹመታቸው መልቀቂያ ካስገቡ በኋላ በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩት ሌንጮ ባቲ ይተኳቸዋል ተብሎ ተጠብቆ ነበር፡፡ ይሁንና አሜሪካ የአምባሳደር ሌኝጮን ሹመት መቃወሟን ተከትሎ ብናልፍ አንዷለም በዋሸንግተን የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ተሹመዋል፡፡ የቀድሞው የአርባምንጭ ዩንቨርሲቲ መምህር ስለሺ በቀለ በአምባሳደርነት ከመሾማቸው በፊት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሆነው ከአምስት ዓመት በላይ አገልግለዋል፡፡ አምባሳደር ሽለሺ በታለቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ለዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ቃለ መጠይቅ በመስጠት የሚታወቁ ሲሆን በኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና…
Read More
ኢትዮጵያ በሶማሊያ መወረሯን እንደማትረሳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገለጹ

ኢትዮጵያ በሶማሊያ መወረሯን እንደማትረሳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገለጹ

የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ታዬ አጽቀስላሴ በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ሚንስትሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት የሶማሊያ መንግሥት ውስጥ ያሉ የተወሰኑ አካላት በኢትዮጵያ ላይ ያልተገባ ስም ማጥፋት ስራ እየሰሩ ነው ብለዋል። ሶማሊያ እንደ ሉዓላዊ ሀገር ከየትኛውም ሀገር ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መመስረት መብቷ ቢሆንም "ይህ የሚሆነው ግን ለሌላ ሀገር ስጋት በማይሆን መልኩ ነው" ሲሉም ሚንስትሩ ተናግረዋል። "በሶማሊያ ያለውን መንግሥት ያቋቋምነው እኛ ነን" ያሉት አምባሳደር ታዬ ይህን ያደረግነው አልሻባብ ስልጣን ቢይዝ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለአካባቢው ሀገራት ስጋት እንደሚሆን ስለምናምን ነውም ብለዋል። የሶማሊያ ሰላም እኛን ይመለከታል፣ ሰላም እንዲመጣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት መስዋዕትነት ከፍሏል፣ አሁንም የሶማሊያ ሁኔታ የሚያሳስበን ድንበር ዘሎ የሚመጣ ትርምስን ስለማንፈልግ ነውም…
Read More
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ጋር ግጭት ውስጥ መግባቷን አመነች

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ጋር ግጭት ውስጥ መግባቷን አመነች

የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር በወቅታዊ የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥታል። የሚንስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም በተለያዩ የዲፕሎማሲ እና ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ቃል አቀባዩ ማብራሪያ ከሰጡባቸው ጉዳዮች መካከል ከሰሞኑ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ልማት ባንክ መክፈል ያለባትን ብድር ከመክፈል ጋር በተያያዘ አለመግባባት ተፈጥሯል የሚለው ጉዳይ ነው። አለመግባባቱ በኢትዮጵያ ገንዘብ ሚንስቴር እና በአዲስ አበባ ካለው የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያ ቢሮ ጋር መካከል ነው የተባለ ሲሆን በተፈጠረው አለመግባባት ምክንያትም ባንኩ ቢሮውን ዘግቶ ሆዷል የሚል ነበር። በሁለቱ አካላት መካከል የተፈጠረው ግጭት ምንድን ነው? ባንኩስ የኢትዮጵያ ቢሮውን ዘግቶ ወጥቷል? በሚል ለአምባሳደር መለስ ዓለም ጥያቄ ከጋዜጠኞች ቀርቦላቸው ነበር። አምባሳደር መለስ በምላሻቸውም "ከአፍሪካ ልማት ባንክ ኢትዮጵያ…
Read More
አዲስ አበባ የሩሲያዊ ደራሲ አሌክሳንደር ፑሽኪንን ሐውልት ዳግም ወደ አደባባይ ልትመልስ መሆኗን ገለጸች

አዲስ አበባ የሩሲያዊ ደራሲ አሌክሳንደር ፑሽኪንን ሐውልት ዳግም ወደ አደባባይ ልትመልስ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ የታዋቂውን ሩሲያዊ ደራሲ ፑሽኪን ሐውልትን ወደ አደባባይ ልትመልስ መሆኗን ገለጸች የሩሲያ ዋና ከተማ ሞስኮ በፈረንጆቹ 2002 ላይ ነበር የታዋቂውን የሩሲያዊ የስነ ጽሁፍ ሰው አሌክሳንደር ፑሽኪንን ሀውልት በስጦታ መልኩ ለአዲስ አበባ የሰጠችው። ይህ ሀውልት ለረጅም ዓመታት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ስር ባለ አንድ አደባባይን የፑሽኪን አደባባይ በሚል የሰየመችው። በዚህ አደባባይ ላይም የፑሽኪን ሐውልት ተተክሎ የቆየ ቢሆንም የትራፊክ መጨናነቅን ለማስቀረት በሚል አደባባዩ ፈርሷል። የአሌክሳንደር ፑሽኪን ሀውልትም ወደ ኢትዮጵያ ሙዚየም ግቢ ውስጥ እንዲቀመጥ ተደርጎ ቆይቷል። የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ እያሱ ሰለሞን ለአልዐይን እንዳሉት የፑሽኪን ሀውልት ወደ አደባባይ ወጥቶ ይተከላል ብለዋል። "ሀውልቱ የሩሲያን እና ኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ክብር…
Read More
ኢትዮጵያ ዲፕሎማሲዋን ከማለዘብ ወደ ማሳመን መቀየሩን ገለጸች

ኢትዮጵያ ዲፕሎማሲዋን ከማለዘብ ወደ ማሳመን መቀየሩን ገለጸች

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም በወቅታዊ የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ በሰሜኑ ጦርነት ውስጥ በነበረችበት ወቅት  የደረሱ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ለመቋቋም "የማለዘብ ዲፕሎማሲ" ስትከተል መቆየቷን የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል። በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ እና ተጨማሪ የዲፕሎማሲ ስራዎች በመሰራታቸው ይደርሱ የነበሩ ጫናዎች መቀነሳቸውን ቃል አቀባዩ ጠቅሰዋል። ይህን ተከትሎም ኢትዮጵያ አሁን ላይ ከማለዘብ ዲፕሎማሲ ወደ ማሳመን ዲፕሎማሲ መመለሷን የተናገሩት አምባሳደር መለስ የተለያዩ የዓለማችን ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለማሻሻል መሪዎቻቸውን ወደ አዲስ አበባ በመላክ ላይ መሆናቸውን አክለዋል። የአፍሪካ መዲና የሆነችው አዲስ አበባ ከተማም ከኒዮርክ እና ጀኔቫ በመቀጠል ሶስተኛዋ የዓለማችን የዲፕሎማሲ ከተማ ይዞታዋ መመለሷን ቃል…
Read More
ኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረትን መግለጫ እንደምትቀበል ገለጸች

ኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረትን መግለጫ እንደምትቀበል ገለጸች

ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ሕብረት ጋር ያላትን ትብብር በአዲስ መልክ እንደገና ለማደስ አበክራ እየሰራች እንደምትገኝም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓ ሕብረት ምክር ቤት ከትናንት በስቲያ ኢትዮጵያን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ዙሪያ ምላሽ አውጥቷል። ሚኒስቴሩ ምክር ቤቱ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ትግበራ ላይ የተገኙ ውጤቶችን ጨምሮ ለሌሎች ጉዳዮች እውቅና መስጠቱን ገልጿል። ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ሕብረት ጋር ያላትን ትብብር በአዲስ መልክ እንደገና ለማደስ አበክራ እየሰራች እንደምትገኝና የምክር ቤቱ መግለጫም ይሄንኑ ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑን አመልክቷል። ሕብረቱ በዘላቂ ግብርናና የምግብ ዋስትና ላይ ያተኮረውን ዓመታዊ የባለብዙ ዘርፍ የድጋፍ ፕሮግራም በድጋሚ ለመጀመር ያሳየውን ዝግጁነት፣ አበዳሪ አገራት ባቋቋሙት የጋራ ማዕቀፍ ስር የሚከናወነው የኢትዮጵያ የዕዳ ሽግሽግ የድርድር ሂደት በአፋጣኝ እንዲቋጭ ያቀረበው ጥሪና…
Read More
የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን ኢትዮጵያ ገቡ

የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን ኢትዮጵያ ገቡ

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝታቸውን በኢትዮጵያ ጀምረዋል። አንቶኒ ብሊንከን በአሁኑ የአፍሪካ ጉብኝታቸው ኢትዮጵያን እና ኒጀርን እንደሚጎበኙ ተገልጿል። ሚንስትሩ በአዲስ አበባ በሚኖራቸው ቆይታ በፌደራል መንግሥት እና ህወሀት መካከል በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተፈረመውን የሰላም ስምምነት አፈጸጸም ዙሪያ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር እንደሚመክሩ ተገልጿል። ከዚህ በተጨማሪም ከጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ፣ ከሲቪል ሶሳይቲ እና የፖለቲካ አመራሮች ጋር እንደሚመክሩም ይጠበቃል። በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት መጀመሩን ተከትሎ ግንኙነታቸው ሻክሮ የቆዩት ኢትዮጵያ እና አሜሪካ የአንቶኒ ብሊንከን ጉብኝት ለሁለቱ ሀገራት ግንኙነት መሻሻል አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ባሳለፍነው ህዳር በዋሽንግተን በተካሄደው የዩኤስ-አፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ላይ መሳተፋቸው ይታወሳል። ፕሬዝደንት ጆ ባይደን ኤርቪን ጆሴፍ ማሲንጋን በኢትዮጵያ የአሜሪካ…
Read More