UN

ተመድ ኢትዮጵያ ወደ ሀገር አቀፍ ግጭት እያመራች ነዉ ሲል አስጠነቀቀ

ተመድ ኢትዮጵያ ወደ ሀገር አቀፍ ግጭት እያመራች ነዉ ሲል አስጠነቀቀ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ኢትዮጵያ ወደ ሀገር አቀፍ ግጭት እያመራች ነዉ ሲል አሳዉቋል። በአማራ እና ኦሮሚያ ክልል ያለዉም ግጭት ተበራክቷል ያለው ተመድ የግጭቶች መበራከት ኢትዮጵያን ወደ ሀገር አቀፍ መጠነ ሰፊ ግጭት ሊወስዳት ይችላል ሲልም አስጠንቅቋል። ከዚህ በተጨማሪም በአማራ ክልል ያለዉን ወቅታዊ ሁኔታ በማስመልከት ፤ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የጅምላ እስር እና እንግልት እየተፈጸመ እንደሆነም አስታውቋል። ድርጅቱ በመግለጫው አክሎም በክልሉ ፤ በመንግስት ቢያንስ አንድ ጊዜ የሰዉ አልባ አዉሮፕላን ጥቃት መፈጸሙን የደረሱኝ ሪፖርቶች ያመለክታሉ ሲልም ጠቅሷል። በአማራ ክልል በርከታ ከተሞችም ከሲቪል አስተዳደር ዉጪ በመሆን በወታደራዊ ስርዓት ስር ወድቀዋል ተብሏል። በአማራ ክልል የተፈጠረውን ጦርነት ተከይሎ ካሳለፍነው ሀምሌ ወር ጀምሮ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መደንገጉን ተከትሎ…
Read More
ኢትዮጵያ በአማራ ክልል ያለውን ሁኔታ ለተመድ የሰብዓዊ ድርጅቶች ማብራሪያ ሰጠች

ኢትዮጵያ በአማራ ክልል ያለውን ሁኔታ ለተመድ የሰብዓዊ ድርጅቶች ማብራሪያ ሰጠች

ተቀማጭነታቸውን አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ላደረጉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ተቋማትተወካዮች በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ ተሰጠ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፖለቲካና ኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር መስጋኑ አርጋ፤ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ በተለይም በአማራ ክልል ስላለው የሰብዓዊ ሁኔታ ለተወካዮቹ ገለጻ አድርገዋል። በዚህም የኢትዮጵያ መንግሥት አጠቃላይ የሰብአዊ ሁኔታን ለማሻሻል እና ከእርዳታ ድርጅቶች ጋር በመሆን ምግብን ጨምሮ የእርዳታ አቅርቦትን ለማፋጠን ያለውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል፡፡ ሚኒስትር ዴኤታው የአማራ ክልል ወደ ቀድሞ ሁኔታው እየተመለሰ መሆኑን በማንሳት፤ በአብዛኛዎቹ ቦታዎች አዲስ የክልል አስተዳደር ተቋቁሞ ተቋርጠው የነበሩ መሠረታዊ አገልግሎቶችም ዳግም መጀመራቸውን አስረድተዋል። አምባሳደር ምስጋኑ አያይዘውም፤ አፋጣኝ የሰብአዊ እርዳታ በሚያስፈልጉባቸው አካባቢዎች ያለውን ኹኔታ በተለይም የምግብ አቅርቦትን የሰብአዊ እርዳታ ድርጅቶች በፍጥነት እንዲከታተሉ…
Read More
ኢትዮጵያ ኤርትራዊያንን ከማፈናቀል እንድትታቀብ ተመድ ጠየቀ

ኢትዮጵያ ኤርትራዊያንን ከማፈናቀል እንድትታቀብ ተመድ ጠየቀ

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኢትዮጵያ በሰኔ ወር መጨረሻ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኤርትራውያንን አፈናቀላለች ሲል ገልጿል፡፡ ተመድ ኢትዮጵያ  የኤርትራ ስደተኞችን እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን፤ የስደተኞችን ሕግን በመጣስ እንዲሁም ክስ ሳይኖርባቸው በዘፈቀደ የማሰር እና የማፈናቀል ተግባሯን በአስቸኳይ እንደታቆም ነው ያሳሰበው። ድርጅቱ ወደ ሌላ አገር ጥገኝነት ጠይቀው የገቡ ስደተኞችን በጅምላ ማባረርና በዘፈቀደ ማሰር በዓለም አቀፍ ሕግ የተከለከለ ነው ሲልም ገልጿል፡፡ በዚህም የመንግሥታቱ ድርጅት ኢትዮጵያ እያደረገችው ያለውን ጥገኝነት ጠያቂዎችን የማሰቃየት፤ በግዳጅ የማፈናቅልና የሰብአዊ መብት ረገጣ አውግዟል። ኢትዮጵያ በሱዳን ጥገኝነት ጠይቀው ሲኖሩ የነበሩና በጦርነቱ ምክንያት ወደ አገሪቷ የገቡ ኤርትራውያን ላይ ጭካኔ የተሞላበት ኢ-ሰብአዊ አያያዝ እየተፈጸመች ነው የተባለ ሲሆን፤ ይህም ዓለም አቀፋዊ የሰብአዊ መብት ስምምነቶችን ሙሉ ለሙሉ የጣሰ ድርጊት…
Read More
ተመድ በቶርች ጉዳይ ኢትዮጵያን ሊገመግም መሆኑን አስታወቀ

ተመድ በቶርች ጉዳይ ኢትዮጵያን ሊገመግም መሆኑን አስታወቀ

የተባበሩት መንግታት ድርጅት በፈረንጆቹ 1984 ላይ በእስረኞች የሚፈጸሙ ስቃዮችን ወይም ቶርቸርን ለመከላከል በማሰብ ስምምነት አዘጋጅቶ ነበር። ይህን ስምምነት ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ የዓለማችን ሀገራት የተቀበሉት ሲሆን ትግበራው ግን ከቦታ ቦታ ይለያያል። የዚህ ስምምነት አዘጋጅ የሆነው ተመድ ስምምነቱን የተቀበሉ ሀገራት ህጉን እንዴት እየተገበሩት እንደሆነ ሊገመግም መሆኑን ለዓልዐይን በላከው መግለጫ አስታውቋል። ኢትዮጵያ ፣ ኮሎምቢያ፣ ብራዚል፣ ካዛኪስታን፣ ስሎቫኪያ እና ሉግዘምበርግ ደግሞ የሚገመገሙ ሀገራት ናቸው ተብሏል። 10 አባላት ያሉት የተመድ ገለልተኛ የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ሀገራቱን በጀኔቫ እንደሚገመግሙም ተገልጿል። ይህ የባለሙያዎች ቡድንም የጸረ ቶርቸር ህግ ትግበራው ግምገማው የተገምጋሚ ሀገራት ተወካዮች፣ የሰብዓዊ መብት ተቋማት እና ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸው አካላት ይገኛሉ ተብሏል። ግምገማውም ከሚያዚያ 9 ቀን እስከ…
Read More