Uncategorized

ሶስተኛው የህዳሴው ግድብ ድርድር በካይሮ እንደሚካሄድ ተገለጸ

ሶስተኛው የህዳሴው ግድብ ድርድር በካይሮ እንደሚካሄድ ተገለጸ

ባሳለፍነው ሐምሌ ወር ላይ በሱዳን ለተከሰተው ጦርነት እልባት ለመፈለግ በሚል በካይሮ በተካሄደው የጎረቤት ሀገራት መድረክ ላይ ለመሳተፍ ወደ ስፍራው ያቀኑት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ ጋር የህዳሴው ግድብ የሶስትዮሽ ድርድርን ለማስቀጠል መስማማታቸው ተገልጾ ነበር፡፡ በዚህ ስምምነት መሰረት ከሶስት ሳምንት በፊት የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን የግድቡ ተደራዳሪ የቴክኒክ ባለሙያዎች በግብጽ ካይሮ ተገናኝተው ተወያይተዋል። እንዲሁም ሁለተኛው ዙር የቴክኒክ ባለሙያዎች ውይይት ደግሞ ባሳለፍነው ቅዳሜ እና እሁድ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን የግድቡ ተደራዳሪዎች፣ ባለሙያዎች እና ዲፕሎማቶች የተሳተፉበት ይህ ውይይት ከተጠናቀቀ በኋላ የሁለቱም ሀገራት በጉዳዩ ዙሪያ መግለጫ አውጥተዋል፡፡ የግብጽ ውሃ እና መስኖ ሚኒስትር ሀኒ ስዌለም እንዳሉት በአዲስ አበባ የተካሄደው ድርድር…
Read More
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአንዋር ሶሳ ምትክ አዲስ ሀላፊ ሾመ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአንዋር ሶሳ ምትክ አዲስ ሀላፊ ሾመ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አዲስ ሀላፊ ተሾመለት። ላለፉት ሁለት ዓመታት ሳፋሪኮም ኢትዮጵያን በሀላፊነት ሲመሩ የቆዩት አንዋር ሶሳ መልቀቃቸው ይታወሳል። ድርጅቱ ባሳለፍነው ሳምንት እንዳለው አንዋር ሶሳ ከቀጣዩ ወር ጀምሮ በሀላፊነታቸው እንደማይቀጥሉ አስታውቋል። ይህን ተከትሎም የቀድሞው የኤምቲኤን ኡጋንዳ ሀላፊ የነበሩት ዊም ቫንሄልፑት አንዋር ሶሳን ተክተው ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ ሮይተርስ ዘግቧል። በዜግነት ቤልጂየማዊ የሆኑት አዲስ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ስራ አስፈጻሚ ከቀጣዩ መስከረም ጀምሮ ድርጅቱን መምራት ይጀምራሉ። ሳፋሪሎም ኢትዮጵያ በኤምፔሳ አማካኝነት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ለመስጠት ፈቃድ ማግኘቱ ይታወሳል። በፈረንሳይ የኢትዮጵያ የቀድሞ አምባሳደር የሆኑት ሔኖክ ተፈራን የውጭ ግንኙነት ሀላፊ አድርጎ የሾመው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከሶስት ሚሊዮን በላይ ደንበኞች ማፍራቱንም አስታውቋል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከኢትዮ ቴሌሎም ብርቱ…
Read More