05
Dec
በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ባለፉት ሶስት ቀናት የተፈጠሩ አለመረጋጋቶች ነዋሪዎችን እንዳስጨነቃቸው ተናግረዋል፡፡ ያነጋገርናቸው የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች እንዳሉት የትግራይ ታጣቂዎች ከነ ትጥቃቸው ወደ ከተማዋ በመግባት ሲንቀሳቀሱ የታዩ ሲሆን በተለይም የክልሉ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት አካባቢ ያለው ሁኔታ አስፈሪ ነው ብለዋል፡፡ ለደህንነቱ በመስጋት ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ ነዋሪ እንዳለው ከሆነ "ከዚህ ቀደምም ብዙ አስተያየት ሰጥተናል፤ ሰሚ ግን የለም። ህዝቡ ጦርነት ሰልችቶናል ፤ እስካሁን ያደረጋችሁት የእርስ በርስ ግጭት ይበቃችኋል ብሏል። ገላጋይ ነው ያጣነው " ብለዋል። ከትናንት በስቲያ ጀምሮ የደመወዝ ይከፈለን የሚሉ ጥያቄዎችን ይዘው ወደ ከተማዋ ገብተዋል የተባሉት ታጣቂዎች ላለፉት ሁለት ቀናት የፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤትን እንደከበቡ ናቸውም ተብሏል፡፡ ታጣቂዎቹ ከከልሉ ፕሬዝዳንት ጸህፈት ቤት በተጨማሪም የክልሉ መንግስት…