Electioninethiopia

የብልጽግና ፓርቲ ከነጋዴው ማህበረሰብ በአስገዳጅነት ገንዘብ መሰብሰቡን እንዲያቆም ተጠየቀ

የብልጽግና ፓርቲ ከነጋዴው ማህበረሰብ በአስገዳጅነት ገንዘብ መሰብሰቡን እንዲያቆም ተጠየቀ

ለሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ በምርጫው የሚሳተፍ ሀገር አቀፍ እና ክልላዊ ፓርቲዎች በምርጫው ላይ ጉልህ ተሳትፎ ለማድረግ የድርሻቸውን ዝግጅት እያደረጉ ይገኛሉ። ከዝግጅቶቻቸው መካከልም ዋነኛው ለምርጫው የሚያስፈልጋቸውን ገንዘብ እና ሀብት ከአባላቶቻቸው እና ከደጋፊዎቻቸው በተቀመጠው የህግ አግባብ መሰረት ማሰባሰብ አንዱ መሆኑን ኢዜማ ገልጿል። ይህ የገንዘብ እና ቁሳቁስ ማሰባሰብ ሂደት የአገሪቱን የፋይናንስ አሰራር ስረዓት እንዲሁም ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፓለቲካ ፓርቲዎች የሀብት አሰባሰብን በተመለከተ ያስቀመጣቸውን ጥብቅ የህግ ድንጋጌዎች ባከበረ መልኩ መሆን እንዳለበትም ፓርቲው አስታውቋል። ኢዜማ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ ብልፅግና ፓርቲ የህግ ድንጋጌዎች በጣሰ መልኩ በማንአለብኝነት መንፈስ ከፍተኛ ገንዘብ አባል ካልሆኑ ነጋዴዎች እና ባለሀብቶች በግዳጅ እያሰባሰበ እንደሆነ ደርሼበታለሁ ብሏል። "16 ሚሊዮን አባል አለኝ የሚለው ብልፅግና…
Read More
ራያ እና ወልቃይት አካባቢ ከትግራይ ክልል ውጪ ሆነው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድ ተወሰነ

ራያ እና ወልቃይት አካባቢ ከትግራይ ክልል ውጪ ሆነው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድ ተወሰነ

የፌዴሬሽን ምክር ቤት በአማራ እና ትግራይ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ በሚያነሱባቸው አካባቢዎች ምርጫ እንዲካሄው ውስኗል ተብሏል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ የካቲት 16፣ 2018 ባወጣው መግለጫ ከዚህ በፊት በትግራይ ክልል ስር ሆነው ምርጫ ሲካሄድባቸው የነበሩ ምርጫ ክልሎች ከክልሉ መንግስት ውጪ ሆነው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድባቸው መወሰኑን የሚገልጽ ደብዳቤ እንደደረሰው ገልጿል፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብቻ ይካሄድባቸዋል ተብለው በቦርዱ መግለጫ ላይ የተጠቀሱት ምርጫ ክልሎች ሁመራ፣ አዲረመጽ፣ ኮረምኦፍላ ፣ ጠለምት እና ራያ አላማጣ ምርጫ ክልሎች እንደሆኑም ቦርዱ አስታውቋል፡፡ ቦርዱ አክሎም የክልል ምክር ቤት ምርጫ በአካባቢዎቹ ላይ የተነሳባው የይገባኛል ውዝግብ ጥያቄ በህገ መንግስት ውሳኔ መሰረት ሲፈታ እንደሚካሄድ ቦርዱ አስታውቋል።የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳድር በበኩሉ…
Read More
የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምጽ መስጫ ቀን ግንቦት 24 እንዲሆን ቀረበ

የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምጽ መስጫ ቀን ግንቦት 24 እንዲሆን ቀረበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛ ጊዜ የሚካሄደውን ሀገር አቀፍ ምርጫ፤ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ለማድረግ ምክረ ሃሳብ አቅርቧል። የምርጫ ውጤት ለህዝብ ማሳወቂያ ቀን ደግሞ ሰኔ 3 ቀን እንደሚሆንም ቦርዱ አስታውቋል። ሰባተኛው ሀገር አቀፍ ጠቅላላ ምርጫ ለማድረግ በዝግጅት ላይ የሚገኘው ብሔራዊው ምርጫ ቦርድ በምርጫው የጊዜ ሰሌዳ ዙሪያ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይት አድርጓል። ከ60 በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች በተሳተፉበት በዚህ ውይይት ላይ በምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ላይ የጦፈ ውይይት መደረጉ ተገልጿል። መገናኛ ብዙሃን ባልተገኙበት በዚህ የውይይት መድረክ ላይ፤ ምርጫ ቦርድ የሰባተኛውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ዝርዝር የጊዜ ሰሌዳን ለፓርቲዎች ለውይይት አቅርቧል። ለውይይት በቀረበው የጊዜ ሰሌዳው መሰረትም ህዳር ወር ውስጥ በምርጫ መወዳደር የሚፈልጉ…
Read More
አምስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ብልጽግና ፓርቲን ለማሸነፍ ህብረት ፈጠሩ

አምስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ብልጽግና ፓርቲን ለማሸነፍ ህብረት ፈጠሩ

ፓርቲዎቹ "ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት" የተሰኘ የቅንጅት ፖርቲ መመስረታቸውን ገልጸዋል። ላለፉት ሥስት ዓመታት በትብብር በጋራ ሲሠሩ የቆዩት አምስት የፖለቲካ ድርጅቶች ቅንጅት መመሥረታቸውን በዛሬው ዕለት አስታውቀዋል። የቅንጅቱ ስያሜም "ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት" መሆኑን በዛሬው የመስራች ጉባኤ ላይ ተገልጿል። የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ እናት ፖርቲ ፣የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፖርቲ (ኢሕአፓ)፣ አንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ እና አማራ ግዮናዊ ንቅናቄ ናቸው ቅንጅት መመሥረታቸውን አስታውቀዋል። ቅንጅቱንም እንዲመሩ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፕሬዝዳንት አቶ አብርሀም ጌጡ ተመርጠዋል። "ለእናት ፖርቲ ትልቅ ቀን ነው" ያሉት የፖርቲው ፕሬዝዳንት ሰይፈስላሴ አያሌው (ዶ/ር)፤ "ኢትዮጵያ 50 ዓመታት የተበታተነ የፖለቲካ ጎራ መከራ እየወረደበት ላለው ፖለቲካ መፍትሄ የሚሰጥ ቅንጅት ነው" ሲሉ ተናግረዋል። በተናጥል የሚመጣ…
Read More
ኢትዮጵያ የምርጫና ፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ ህጓን አሻሻለች

ኢትዮጵያ የምርጫና ፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ ህጓን አሻሻለች

ሀገራዊ ፓርቲ ለመሆን በስድስት ክልሎች የድጋፍ ፊርማ ማሰባሰብን የሚያስገድደዉ አዋጅ ፀድቋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው ጉባኤ የምርጫ እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ ረቂቅ አዋጅን አጽድቋል። አዋጁ ከነባሩ አዋጁ 1162/2011ዉስጥ የነበሩ 26 አንቀጾችን ያሻሻለ ሆኖ የቀረበ ነዉ ተብሏል። አንድ የፖለቲካ ፓርቲ ሀገራዊ ፓርቲ ሆኖ ለመወዳደር ከ 6 ክልሎች የ60 በመቶ ድጋፍ ፊርማ ማሰባሰብን የሚያስገድድ አንቀፅ ይገኝበታል። ከዚህ ቀደም ሀገራዊ ፓርቲ ለመሆን የአራት ክልሎች የድጋፍ ፊርማ የሚያስፈልግ ሲሆን ይህንን አንቀፅ ለማሻሻል ያስፈለገበት ምክንያት የተጨመሩ ክልሎች መኖራቸዉን ታሳቢ አድርጎ መሆኑን ምክር ቤቱ ገልጿል። በዚህ መሰረት ሀገራዊ ፓርቲ ለመመስረት በስድስት ክልሎች የድርጅት አባል ማፍራት እንዳለባቸዉ የሚያደርግ ነዉ። አንድ የምክር ቤት አባል የሀገራዊ ፓርቲ ምስረታን…
Read More
በኢትዮጵያ አራት ክልሎች ምርጫ መካሄድ ጀመረ

በኢትዮጵያ አራት ክልሎች ምርጫ መካሄድ ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ ቀሪ ምርጫ በሚደረግባቸው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና አፋር ክልሎች እንዲሁም ድጋሚ ምርጫ በሚደረግባቸው በጅግጅጋ 2 እና መስቃንና ማረቆ ምርጫ ክልሎች በዛሬው ዕለት ምርጫ እየተካሄደ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ በ6ኛው ዙር ሀገራዊ ቀሪና ድጋሚ ምርጫ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ድምፅ መስጠት መጀመሩን አስታውቋል። ዛሬ እየተካሄደ ባለው የድምጽ አሰጣጥ ሂደት ላይም 12 የፖለቲካ ፓርቲዎች እየተሳተፉ መሆኑን ከምርጫ ቦርድ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ቀሪና ድጋሚ ምርጫ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በአፋር፣ በሶማሌ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች እየተካሄደ መሆኑንም ነው ቦርዱ ያስታወቀው። ቀሪና ድጋሚ ምርጫ ከሚካሄድባቸው አካባቢዎች አንዱ በአፋር ክልል የሲሆን፤ በክልሉ 4 ዞኖች፣ በ9 የምርጫ ክልሎች እና በ388 የምርጫ…
Read More
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በአራት ክልሎች ምርጫ ሊያካሂድ መሆኑን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በአራት ክልሎች ምርጫ ሊያካሂድ መሆኑን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6 ኛውን ዙር ቀሪና ድጋሚ ጠቅላላ ምርጫ በሚካሄድባቸው አራት ክልሎች ምርጫ እንደሚያካሂድ ገልጿል፡፡ ምርጫ የሚካሄደው በጸጥታ እና በሌሎች ምክንያቶች ምርጫ ያልተካሄደባቸው አካባቢዎች ነው የተባለ ሲሆን የቤንሻንጉል ጉምዝ፤ አፋር፤ ሶማሌ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ 29 የምርጫ ክልሎች ውስጥ እንደሆነም ቦርዱ አስታውቋል፡፡ በዚህ ምርጫ ፕሮግራም ለዘጠኝ የተወካዮች ምክር ቤትና ለሃያ ስድስት የክልል ምክር ቤቶች ምርጫ ለማካሄድ እንደታቀደም ተገልጿል፡፡ ቦርዱ ባወጣው የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ መሰረትም የእጩዎች ምዝገባ ከሚያዝያ 7 እስከ ሚያዝያ 16 ቀን 2016 ዓ/ም ይካሄዳል የተባለ ሲሆን የምረጡኝ ቅስቀሳ ደግሞ ከሚያዚያ 7 እስከ ሰኔ 1 ቀን 2016 ዓ/ም ይካሄዳል፡፡ እንዲሁም የመራጮች ምዝገባ ደግሞ ከሚያዝያ 7 እስከ…
Read More
ኢትዮጵያ ለምርጫ ስርዓት ማጠናከሪያ የ30 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አገኘች

ኢትዮጵያ ለምርጫ ስርዓት ማጠናከሪያ የ30 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አገኘች

ኢትዮጵያ ዘላቂ ዲሞክራሲን ለማስፈን የሚያስችላትን የምርጫ ስርአት እንድታጠናክር ለማግዝ የሚውል የ30 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዶላር የፋናንስ ድጋፍ ስምምነት ፈርማለች፡፡ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚኒስቴር፣ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና የተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት መካካል ተፈርሟል፡፡ የበጀት ድጋፉ የምርጫ ቦርድ ተቋማዊ መዋቅርን ለማጠናከር ነፃ፣ ፍትሃዊ፣ አሳታፊ ፣ተአማኒና ደረጃውን የጠበቀ ምርጫና ህዝበ ውሳኔ እንዲያካሂድ ተቋሙን ማጠናከር፣ ከሲቪክ ተቋማት በጋራ በመሆን በምርጫ ሂደት የሴቶችና ወጣቶች ተሳትፎን ለማሳደግ ይውላል ተብሏል፡፡ እንዲሁም የበጀት ድጋፉ በኢትዮጵያ ነፃ ፍትሀዊ እና ተአማኒ ምርጫ እንዲያከሂድ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር እንደሚውልም የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ይህ የበጀት ድጋፍ ፕሮጀክት በሚቀጥሉት አራት አመታት ውስጥ ተግባራዊ የሚደረግ ሲሆን የሀገሪቱን የምርጫ ስርአት በማጠናከር ዘላቂ ዴሞክራሲን ለማስፈን አስተዋጽኦ…
Read More
ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሀላፊነት ለቀቁ

ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሀላፊነት ለቀቁ

ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሀላፊነት ለቀቁ ከ2011 ዓ.ም ታህሳስ ወር ጀምሮ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሆነው ስራ የጀመሩት ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ በጠየና ምክንያት የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ሰማያዊ ማረጋገጫ ባለው የፌስቡክ ገጻቸው ላይ ገልጸዋል፡፡ “ባለፉት  አራት አመት ከስድስት ወራት ሶስት ህዝበ ውሳኔዎችን እና አገራዊ ምርጫን በማካሄድ እና ፓለቲካ ፓርቲዎችን በማስተዳደር የተሰጡኝን ሃላፊነቶች ህጋዊነት ፍትሀዊነት እና ቅንነትን በተከተለ ሁኔታ ለማከናወን ስጥር ቆይቻለሁ” ብለዋል። “ሆኖም ጤናዬን በሚገባ ለመጠበቅ የረጅም ጊዜ እረፍት የሚያስፈልገኝ ሆኖ በመገኘቱ ከ ነሀሴ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቦርድ ሰብሳቢነቴ በገዛ ፍቃዴ  መልቀቄን ለተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ጽህፈት ቤት ሰኔ 5 ቀን 2015 ዓ.ም አሳውቄያለሁ” ሲሉም…
Read More