Amhara

ኢትዮጵያ የጣና ደሴት እና ገዳማትን በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ ዘመቻ ጀመረች

ኢትዮጵያ የጣና ደሴት እና ገዳማትን በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ ዘመቻ ጀመረች

የጣና ሀይቅ ደሴትና ገዳማት በአለም አቀፍ የቅርስ መዝገብ እንዲሰፍሩ የሚያስችለዉ ሰነድ ለዮኔስኮ ተልኳል። በአማራ ክልል የሚገኙ የመስህብ ሀብቶችን በማልማትና በማስተዋወቅ የባህልና ቱሪዝም ኢንዱስትሪውን በማሳደግ የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ  አስታውቋል። የቢሮው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት አቶ አበበ እምቢአለ እንደተናገሩት በክልሉ የሚገኙ በርካታ የመስህብ ቦታዎች እንደመኖራቸው የጣና ሀይቅ እና አካባቢውን በዮኔስኮ አለም አቀፍ ቅርስነት ለማስመዝገብ ጥረቶች ሲደረጉ ቆይተዋል። ከዚህ ቀደም  የጣና ሀይቅ ደሴቶች በብዛ ህይወት ቅርስነት የተመዘገበ መሆኑን ገልፀው በአሁኑ ወቅት ይህ ስፍራ በአለም አቀፍ ቅርስነት እንዲመዘገብ ለማድረግ በተዘጋጀዉ ሰነድ ዙሪያ ማስተካከያ መደረጉን ተናግረዋል። ሰነዱን አስመልክቶ አስተያየት የመስጠትና ተጨማሪ ግብዓቶችና ማስተካከያዎችን የማዘጋጀት ስራ ሲሰራ እንደቆየ የገለፁት…
Read More
የአማራ ክልል ሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ተጠናቀቀ

የአማራ ክልል ሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ተጠናቀቀ

የአማራ ክልል የማህበረሰብ ተወካዮች ሲያካሄዱት የቆየው የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ተጠናቋል፡፡ የአማራ ክልል የማህበረሰብ ተወካዮች ካለፈው እሁድ ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት ሲያካሄዱት የቆየው የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት መጠናቁን ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ የማህበረሰብ ተወካዮቹ፤ በመጪዎቹ ቀናት ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በሚደረግ የምክክር ሂደት የሚሳተፉ 270 ወኪሎቻቸውንም መርጠዋል። በአማራ ክልል ዋና ከተማ ባህር ዳር በተካሄደው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ከ263 ወረዳዎች የተመረጡ ከ4,500 በላይ የሚሆኑት የማህበረሰብ ተወካዮች ተሳትፈዋል፡፡ አስር የማህበረሰብ ክፍሎችን የወከሉት እነዚህ የሀገራዊ ምክክር ተሳታፊዎች፤ በባህርዳር ከተማ በነበራቸው ቆይታ ከዘጠኝ እስከ 12 አባላት በሚገኙባቸው ቡድኖች ተከፋፍለው በአበይት ክልላዊ እና ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ሲወያዩ ቆይተዋል። ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን…
Read More
መንግሥት በአማራ ክልል የተናጥል የተኩስ አቁም እንዲያውጅ ተጠየቀ

መንግሥት በአማራ ክልል የተናጥል የተኩስ አቁም እንዲያውጅ ተጠየቀ

እስረኞች እንዲፈቱና በክልሉ ያለው ግጭት እንዲቆምም ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ጥሪ አቅርቧል በሀገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕሮፌሰር) የተመራ የኮሚሽኑ ልዑክ ወደ አማራ ክልል ባህርዳር ከተማ አቅንቶ ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር ውይይት አድርጓል። የኮሚሽኑ ልዑክ ወደ አማራ ክልል ያቀናው የአማራ ክልል የአጃንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ በሚካሄድበት አስቻይ ሁኔታ ላይ ከክልሉ መንግስት ጋር ለመነጋገር ነው። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ በተገኙበት በዚህ ውይይት የኮሚሽኑ የእስካሁን ስራዎች በዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ(ፕሮፌሰር) ቀርቦ የክልሉ አመራሮች ስለ ኮሚሽኑ የስራ እንቅስቃሴ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ተደርጓል። ከኮሚሽኑ የቅርብ ጊዜ የስራ እቅዶች መካከል አንዱ በአማራ ክልል የአጀንዳ ልየታ የምክክር ምዕራፍ ማካሄድ ስለመሆኑ የኮሚሽኑ…
Read More
አምንስቲ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ ላይ ዓለም አቀፍ ጫና እንዲደረግ ጠየቀ

አምንስቲ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ ላይ ዓለም አቀፍ ጫና እንዲደረግ ጠየቀ

አምነስቲ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ አማራ ክልል እየተፈጸመ ነው ያለውን የጅምላ እስራት ለማስቆም አስቸኳይ አለም አቀፍ እርምጃ እንዲወሰድ ጥሪ አቅርቧል። ድርጅቱ የሀገሪቱ መንግስት በክልሉ ሰፊ የእስር ዘመቻ ከጀመረበት መስከረም 2024 ጀምሮ አራት ወራት መቆጠራቸውን አመላክቷል፡፡ አምነስቲ ባወጣው መግለጫ እ.ኤ.አ ሴፕቴምበር 28 ቀን 2024 የኢትዮጵያ ፌዴራል እና የአማራ ክልል የጸጥታ ሃይሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ግለሰቦችን ወደ አራት የጅምላ እስር ቤቶች በማጓጓዝ በክልሉ ውስጥ ማሰራቸውን ገልጿል። እስር ከተፈጸመባቸው መካከል ዳኞች፣ አቃቤ ህጎች፣ ፖለቲከኞች እና ምሁራንን ጨምሮ የፍትህ አካላት ይገኙበታል ተብሏል። የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምስራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ቀጠና ዳይሬክተር ቲጌሬ ቻጉታህ የአለም አቀፉ ማህበረሰብ ለጉዳዩ የሰጠውን ትኩረት ማነስ ተችተዋል፡፡ ዳይሬክተሩ "በአማራ ክልል በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በዘፈቀደ…
Read More
በአማራ ክልል በጦርነት የወደሙ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት 100 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል ተባለ

በአማራ ክልል በጦርነት የወደሙ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት 100 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል ተባለ

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አንዳስታወቀው ከሰሜኑ ጦርነት ጀምሮ አሁን በክልሉ ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት በርካታ ትምህርት ቤቶች ተጎድተዋል። ለአብነትም በምሥራቅ ጎጃም ዞን ከ400 በላይ ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ መውደማቸውን ቢሮው ጠቅሷል። በአጠቃላይ በክልሉ ጉዳት የደረሰባቸውን ትምህርት ቤቶች ወደ አገልግሎት ለመመለስ 112 ቢሊየን ብር ያስፈልጋልም ተብሏል። ቢሮው ባስጠናው ጥናት መሠረት ይህ ገንዘብ ትምህርት ቤቶችን ከመገንባትና መጠገን በተጨማሪ ተጓዳኝ የትምህርት ሥራዎችን ለማከናወን የሚውል ነው፡፡ የፌደራል መንግሥት የክልል ልዩ ሀይሎችን መልሼ አደራጃለሁ ካለበት ሚያዝያ 2015 ዓ.ም ጀምሮ በአማራ ክልል በመንግስት እና ፋኖ ታጣቂዎች የተጀመረው ጦርነት እንደቀጠለ ይገኛል። በዚህ ጦርነት ምክንያት ከስድስት ሚሊዮን በላይ ህጻናት ከትምህርት ውጪ እንደሆኑም ተገልጿል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)…
Read More
ኢህአፓ መንግስት በሚፈጽማቸው የድሮን ጥቃቶች ሰላማዊ ዜጎችን እየገደለ ነው ሲል ከሰሰ

ኢህአፓ መንግስት በሚፈጽማቸው የድሮን ጥቃቶች ሰላማዊ ዜጎችን እየገደለ ነው ሲል ከሰሰ

የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ “የዜጎችን ህይወት የመጠበቅ ሃላፊነት ያለበት መንግሥት ቢሆንም በሚያሰማራቸው የጸጥታ ሃይሎችና የአገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ጭምር የዜጎች ህይወት በበርካታ የሀገሪቱ ክፍሎች እንደቅጠል እያረገፈ ይገኛል” ብሏል፡፡ ኢሕአፓ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ህገመንግሥቱን የመንግሥት አካላት ራሳቸው ካላከበሩት እንዴት ሊያስከብሩት ይችላሉ “በንጹሀን ዜጎች ላይ የሚደረጉት ግድያዎች ይቁሙ” ሲል አሳስቧል፡፡ እንዲሁም የተለያዩ የመንግስት መገናኛ ብዙሀን ከመዘገብ ቢቆጠቡም በውጪ የመገናኛ ብዙሀን ጭምር ጥቃቱ መፈጸሙን እየገለጹ መሆኑን እና ፓርቲውም አጣርቻለሁ ያለውን በየክልሉ የደረሱትን ጥቃቶች አስታውቋል፡፡ ፓርቲው አጣርቻለው ባለው መሰረት ኦሮሚያ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች የሚደርሱ ጥቃቶች የሟቾችን ቁጥር እያሻቀበ መሆኑን እና ጥቃት ከተፈጸመባቸው ውስጥም ነፍሰጡሮች፣ የጤና ባለሙያዎች እና በትምህርት ቤት ውስጥ የነበሩ ተማሪዎች እንደሚገኙበት…
Read More
አቃቢ ህግ ለሽብር ወንጀል ተከሳሾች 96 ምስክሮች እንዳሉት ገለጸ

አቃቢ ህግ ለሽብር ወንጀል ተከሳሾች 96 ምስክሮች እንዳሉት ገለጸ

በእነ ዶክተር ወንደሰን አሰፋ መዝገብ ስር ክስ የተመሰረተባቸው ተጠርጣሪዎች ዛሬ ልደታ በሚገኘው ፍርድ ቤት ችሎት ቀርበዋል፡፡ በዚህ መዝገብ ስር ክስ ከተመሰረተባቸው እና በማረሚያ ቤት ከሚገኙ 23 ተጠርጣሪዎች መካከል ዶክተር ወንደሰን አሰፋ፣ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ፣ ዳዊት በጋሻው፣ መስከረም አበራ፣ ገነት አስማማው እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡ በዚህ መዝገብ ስር 51 ተጠርጣሪዎች የሽብር ወንጀል ለመከላከል የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1176/12 ጥሰዋል በሚል የሽብር ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በአዋጁ አንቀጽ 3/2 ሀ ላይ የተደነገገውን በመተላለፍ የሽብር ወንጀል ፈጽመዋል የሚል ክስ እንደደረሳቸው የተጠርጣሪዎች ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ ለአል ዐይን ተናግረዋል፡፡ አቃቢ ህግ ባሳለፍነው ሰኞ ያሻሻለውን ክስ ለተጠርጣሪዎች እንዲደርሳቸው ያደረገ ሲሆን የተከሳሾችን እምነት ክህደት ቃል ለመቀበል በወቅቱ ባለመሟላታቸው ለዛሬ ህዳር…
Read More
አሜሪካ በአማራ ክልል በመካሄድ ላይ ያለው ግጭት አሳስቦኛል አለች

አሜሪካ በአማራ ክልል በመካሄድ ላይ ያለው ግጭት አሳስቦኛል አለች

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር በስልክ መወያየታቸው ተገልጿል። “በኢትዮጵያ በመካሄድ ላይ ያሉ የእርስ በርስ ግጭቶች እልባት እንዲያገኙ የፖለቲካ ውይይት ወሳኝነት አለው” ሲሉ አንቶኒ ብሊንከን ከጠ/ሚኒስትር አብይ ጋር ባደረጉት የስልክ ውይይት ወቅት መናገራቸው የመስሪያ ቤታቸው መግለጫ አመላክቷል። አሜሪካ “በአማራ ክልል በመካሄድ ላይ ያለው ግጭት ያሳስባታል” ሲሉ መናገራቸውን በመግለጫው ላይ ተገልጿል። አንቶኒ ብሊንከን ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ጋር በስልክ ያወሩት በፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት ዙሪያ እንደነበር ጸ/ቤታቸው ጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። አንቶኒ ብሊንከን “ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነቱ ተግባራዊ እንዲደረግ ለምታደርገው ጥረት ሀገራቸው እገዛ ለማድረግ ዝግጁ ናት” ሲሉ መናገራቸውን መግለጫው ጠቁሟል። የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር…
Read More
ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ተፋናቃዮችን ደህንነት ማስጠበቅ የሚያስችል ህግ እንደሌላት ተገለጸ

ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ተፋናቃዮችን ደህንነት ማስጠበቅ የሚያስችል ህግ እንደሌላት ተገለጸ

የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በሚገኙባቸው መጠለያዎች ታጣቂዎች ሰርገው እየገቡ ጥቃት መፈጸማቸው ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ዙሪያ ለአንድ ዓመት ያደረገውን ሪፖርት ፋ አድርጓል፡፡ ተቋሙ ከሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. እስከ ሰኔ ወር 2016 ዓ.ም. ድረስ ያለውን ጊዜ የሚሸፍን ሦስተኛውን የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ባለ 52 ገጽ ሪፖርት  ይፋ አድርጓል፡፡ ይህ ሪፖርት የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታን በተመለከተ የለያቸውን መልካም ጅማሮዎች፣ አሳሳቢ ሁኔታዎችን እና ምክረ ሐሳቦችን አካቷል። ኢሰመኮ በአማራ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በጋምቤላ፣ በሐረሪ፣ በኦሮሚያ፣ በሶማሊ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ እና በትግራይ ክልሎች በግጭት እና በተፈጥሮ አደጋ መንስኤዎች የተፈናቀሉ ከ333 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን፣ ተመላሾችን እና ወደ ሌላ ቦታ እንዲሰፍሩ የተደረጉ ተፈናቃዮችን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል እና…
Read More
የአማራ ዳኞች ማህበር የታሰሩ አባላቱ እንዲፈቱ ጠየቀ

የአማራ ዳኞች ማህበር የታሰሩ አባላቱ እንዲፈቱ ጠየቀ

የፌደራል መንግስት ክልል የክልል ልዩ ሀይሎችን ዳግም አደራጃለሁ በሚል ውሳኔ ካሳለፈበት ሚያዝያ 2015 ዓ.ም ጀምሮ በአማራ ክልል በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች አማካኝነት ጦርነት ተቀስቅሷል፡፡ በክልሉ ተጥሎ የነበረው የአስቸኳይ አዋጅ ከ10 ወራት በኋላ ያልተራዘመ ቢሆንም አሁንም በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ጦርነቶች እየተካሄዱ ናቸው፡፡ ከጦርነቱ ባለፈም በክልሉ ንጹሃን ዜጎች በጅምላ እየታሰሩ መሆኑን የገለጹ ሲሆን ከነዚህ ውስጥም የአማራ ዳኞች ማህበር እና ጤና ባለሙያዎች ማህበር አባላቶቻቸው ለተለያዩ ጉዳቶች መዳረጋቸውን ተናግረዋል፡፡ የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር እንዳለው በክልሉ ያለው የደህንነት ችግር ዳኞች በነጻነት ስራቸውን እንዳይሰሩ እክል መፍጠሩን ገልጾ ባለፉት ቀናት ውስጥም 13 ዳኞች ታስረዋል፡፡ ከታሰሩት ውስጥ አራት ዳኞች ከእስር መለቀቃቸውን የተናገረው ማህበሩ ቀሪ እና በእስር…
Read More