TPLF

የአፍሪካ ህብረት በራያ እና አላማጣ የተከሰተው አዲስ ግጭት እንደሚያሳስበው ገለጸ

የአፍሪካ ህብረት በራያ እና አላማጣ የተከሰተው አዲስ ግጭት እንደሚያሳስበው ገለጸ

የአማራ እና የትግራይ ክልል የይገባኛል ጥያቄ በሚያነሱባቸው የራያ አላማጣ እና አካባቢዋ ግጭቶች መከሰታቸውን ተከትሎ የአፍሪካ ህብረት መግለጫ አውጥቷል። መግለጫው የህብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሀመት በአወዛጋቢዎቹ ራያ አላማጣ፣ ዛታ እና ኦፎላ "በአካባቢው ማህበረሰብ መካከል ያሉ ውጥረቶችን" በትኩረት እየተከታተሉት መሆኑን ገልጿል። በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በተደረሰው የፌደራል መንግስት እና የህወሓት የዘላቂ ሰላም ስምምነት፣ ሁለቱ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ የሚያነሱባቸው "አወዛጋቢ ቦታዎች" በህገመንግስቱ መሰረት እልባት እንዲያገኙ እንደሚደረግ ይጠቅሳል። ሊቀመንበሩ ሁለቱም ወገኖች ግጭት ከማባባስ እንዲታቀቡ እና የአካባቢውን ንጹሃን መፈናቀል እንዲያስቆሙ ጥሪ አቅርቧል። ከአፍሪካ ህብረት በተጨማሪም መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የሰባት ሀገራት ኤምባሲዎች በአማራ እና ትግራይ ከልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ ያጋጠመው አዲስ ግጭት እንዳሳሰባቸው አስታውቀዋል፡፡ የካናዳ፣…
Read More
ከአላማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ከ50 ሺህ አለፈ

ከአላማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ከ50 ሺህ አለፈ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት 50 ሺህ ዜጎች ከራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መፈናቀላቸውን አስታውቋል፡፡ እንደ ድርጅቱ ሪፖርት ከሆነ ከሰሞኑ በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ ባገረሸው ግጭት ምክንያት ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል ብሏል፡፡ ተፈናቃዮቹ በቆቦ፣ ወልደያ እና ሰቆጣ ከተሞች በሚገኙ መጠለያ ጣቢያዎች ላይ እንደተጠለሉም ድርጅቱ አስታውቋል፡፡ በአካባቢው ባለው አለመረጋጋት ምክንያት ተጨማሪ ዜጎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ የገለጸው ድርጅቱ ለተፈናቃዮች ውሃ፣ ምግብ እና ሌሎች ህይወት ማቆያ ድጋፍ በማድረግ ላይ መሆኑንም ገልጿል፡፡ አሁን ላይ ከለጋሽ ተቋማት እና ሀገራት የሚገኘው ድጋፍ እየተሟጠጠ በመሆኑ በአካባቢው ያለው ማህበረሰብ የሚችለውን ድጋፍ እያደረገ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ ለተፈናቃዮቹ መጠለያ፣ የሕክምና አገልግሎት እና ሌሎች መሰረታዊ ድጋፎችን ማድረግ ይገባል…
Read More
ከአላማጣ እና አካባቢው 29 ሺህ ህዝብ መፈናቀሉ ተገለጸ፡፡

ከአላማጣ እና አካባቢው 29 ሺህ ህዝብ መፈናቀሉ ተገለጸ፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት 29 ሺህ ዜጎች ከራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መፈናቀላቸውን አስታውቋል፡፡ እንደ ድርጅቱ ሪፖርት ከሆነ ከሰሞኑ በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ ባገረሸው ግጭት ምክንያት ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል ብሏል፡፡ ተፈናቃዮቹ በቆቦ፣ ሰሜን ወሎ እና ሰቆጣ ከተማ በሚገኙ መጠለያዎች ላይ እንደተጠለሉም ድርጅቱ አስታውቋል፡፡ በአካባቢው ባለው አለመረጋጋት ምክንያት ተጨማሪ ዜጎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ የገለጸው ድርጅቱ ለተፈናቃዮች ውሃ፣ ምግብ እና ሌሎች ህይወት ማቆያ ድጋፍ በማድረግ ላይ መሆኑንም ገልጿል፡፡ አሁን ላይ ከለጋሽ ተቋማት እና ሀገራት የሚገኘው ድጋፍ እየተሟጠጠ በመሆኑ በአካባቢው ያለው ማህበረሰብ የሚችለውን ድጋፍ እያደረገ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ ለተፈናቃዮቹ መጠለያ፣ የሕክምና አገልግሎት እና ሌሎች መሰረታዊ ድጋፎችን ማድረግ ይገባል…
Read More
አፍሪካ ህብረት በፕሪቶሪያ የተፈረመው የኢትዮጵያን የሰላም ስምምነት መገምገም ጀመረ

አፍሪካ ህብረት በፕሪቶሪያ የተፈረመው የኢትዮጵያን የሰላም ስምምነት መገምገም ጀመረ

በዚህ ግምገማ መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት፣ ህወሃት፣ በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሀመር እና ሌሎችም ተገኝተዋል፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ ለሁለት ዓመታት በዘለቀው ጦርነት የአፍሪካ ህብረት በደቡብ አፍሪካ ዋና ከተማ ፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ጦርነቱ መቆሙ ይታወሳል፡፡ ይህ የሰላም ስምምነት ከተፈረመ አንድ ዓመት ያለፈው ሲሆን በስምምነቱ መሰረት ያልተፈጸሙ ጉዳዮች እንዳሉ በሁለቱም ወገኖች ሲነሳ ቆይቷል፡፡ አፍሪካ ህብረት በኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት መካከል የተደረሰውን የፕሪቶሪያ የተኩስ ማቆም ስምምነት አፈፃፀም ስትራቴጂካዊ ግምገማ እያካሄደ መሆኑን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ይፋ አድርገዋል። የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ በኤክስ ገፃቸው ባጋሩት መልእክት የአፍሪካ ህብረት በኢትዮጵያ መንግስት እና በህዝባዊ ወያነ ሓርነት…
Read More
ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ከአራት ዓመት በኋላ ወደ አዲስ አበባ መጡ

ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ከአራት ዓመት በኋላ ወደ አዲስ አበባ መጡ

የትግራይ ክልል የቀድሞ ፕሬዝዳንት ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ከአራት ዓመት በኋላ ወደ አዲስ አበባ መጡ:: ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ኢትዮጵያ ለዓመታት ወደ ጦርነት እንድተገባ የተገደደችበትን የሀገር መከላከያ ሰራዊት ሰሜን እዝ እሳቸው የሚመሩት የትግራይ ልዩ ሀይል እንዲያጠቃ ማድረጋቸው አይዘነጋም፡፡ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን የተገደሉበት እና 28 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ ንብረት የወደመበት ይህ ጦርነት ከአንድ ዓመት በፊት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ቆሟል፡፡ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በዛሬው ዕለት ከአራት ዓመት በኋላ ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ የመጡ ሲሆን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር ፊት ለፊት ተገናኝተዋል፡፡ ደብረጽዮን እና ሌሎች የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ኃላፊዎች ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ጋር በአዲስ አበባ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም…
Read More
ጦርነት እና እግር ኳስ በኢትዮጵያ….

ጦርነት እና እግር ኳስ በኢትዮጵያ….

ቢኒያም ተክለወይኒ እባላለሁ። ትውልዴ ሽረ ነው። ከጦርነቱ በፊት የፕሪሚየር ሊጉ ተካፋይ የሆነው የስሑል ሽረ ዋና ቡድን ተጨዋች ነበርኩ ። ሊብሮ ነኝ ። አሰልጣኝ ዳንኤል ፀሐዬ ዋና አሰልጣኛችን ነበር ። ኳስ እወዳለሁ ። ደጉ ደበበን አደንቃለሁ ። እንደ እርሱ የመሆን ምኞት ነበረኝ ። ተቀራኒ ሆነን ተጫውተናልም:: በኳስ ጨዋታ መከላከልን እወዳለሁ ። አዳነ ሳላ አማኑኤልን ጨምሮ ከብዙ ጎበዝ አጥቂዎች ተፋጥጫለሁ ። ሁሉንም ገትሬ አቁሜያለሁ ። ቡድኔ ጎል እንዳይቆጠርበት በአግባቡ መምራት መከላከል ከስሑል ሽረ ጋር በፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን መሆን የዘወትር ህልሜ ነበር ። ከሽረ ውጭ ሌላ ክለብ አላውቅም ። በኳስ ጨዋታ መንገዴ የእራሴንም የቤተሰቦቼንም ህይወት መቀየር ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተመርጦ መጫወት የሌት ተቀን…
Read More
በትግራይ ክልል ከ200 በላይ የሚሆኑ ፖሊሶች ከስራ ታገዱ

በትግራይ ክልል ከ200 በላይ የሚሆኑ ፖሊሶች ከስራ ታገዱ

በትግራይ የሚገኙ የፖሊስ አባላት ከብልፅግና ፓርቲ ደሞዝ ስትቀበሉ ነበር በሚል እና የትጥቅ ትግሉን አልተቀላቀላቹም በማለት ከስራ እና ከደሞዝ እንዲታገዱ ቅሬታቸውን አቅርበዋል፡፡ እነዚህ ቅሬታ አቅራቢዎች እስከ 30 ዓመት ድረስ በተለያዩ የትግራይ አካባቢ ተመድበው በፖሊስነት ስራ ላይ ተሰማርተው የቆዩ የቀድሞ የትግራይ ፖሊስ አባላት፥ ከስራ እና ደመወዝ ውጭ እንዲሆኑ የተደረጉት ከጦርነቱ ጅማሮ በኃላ ባለው ጊዜ መሆኑ ነግረውናል።  እንደ ፖሊሶቹ ገለፃ በ2013 ዓ.ም ኢትዮጵያ መከላከያ ትግራይን ሲቆጣጠር አቋቁሞት በነበረው ግዚያዊ አስተዳደር ጋር አብራችሁ ሰርታችኋል የመንግስትን ደሞዝም ተቀብላችኋል በሚል መሆኑን ይናገራሉ፡፡ በ2013 ዓ.ም በርሃ የነበረው የህውሀት ምክር ቤት በዶ/ር ድብረፅዮን ፊርማ በተረጋገጠ ደብዳቤ ነባሩን የፖሊስ አባል በመሰረዝ አዲስ ማቋቋሙን በመግለፅ ከህግ ውጪ ያለ ስራ እንዲቀመጡና…
Read More
ኢትዮጵያ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም ግማሽ ቢሊዮን ዶላር ጠየቀች

ኢትዮጵያ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም ግማሽ ቢሊዮን ዶላር ጠየቀች

ኢትዮጵያ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም ግማሽ ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልጋት ገለጸች የቀድሞው ተዋጊዎችን የተሃድሶ ስልጠና ሰጥቶ ወደ ህብረተሰቡ ለመቀላቀል ከ554 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ እንደሚያስፈልግ የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ተናግረዋል፡፡ ኮሚሽነሩ ይህን የተናገሩት ኮሚሽኑ የቀድሞው ተዋጊዎችን መልሶ በዘላቂነት በማቋቋም ረገድ የመገናኛ ብዙሃን ሚናና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጋር ባካሄደው ውይይት ላይ ነው፡፡ የኮሚሽኑ ጽ/ቤት ሃላፊ ገመዳ አለሚ በበኩላቸው ይህ  የገንዘብ መጠን በመነሻነት የታቀደ እንደነበረ የጠቀሱት ኮሚሽነሩ አሁን ላይ ግን ከተጠቀሰው ከፍ ማለቱን ተናግረዋል ። በኢትዮጵያ 372 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎች እንዳሉ የተሀድሶ ማዕከል እና የሀገር መከላከያ ሚንስቴር በጋራ ያጠኑት ጥናት ያስረዳል። የተመዘገበው አሐዝ ይህ ቢሆንም ቁጥር ሊያሻቅብ…
Read More
የትግራይ እና አማራ ክልል አመራሮች ከሁለት ዓመት ደም አፋሳሽ ጦርነት በኋላ ተገናኙ

የትግራይ እና አማራ ክልል አመራሮች ከሁለት ዓመት ደም አፋሳሽ ጦርነት በኋላ ተገናኙ

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳድር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ወደ ባህርዳር ያቀኑ ሲሆን ከአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ይልቃል ከፋለ ጋር ተወያይተዋል፡፡ አቶ ጌታቸው ረዳ እና ልዑካቸው ከአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ጋር እንዲሁም ከህብረተሰቡ ከተውጣጡ ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል። በዚህ ውይይት ላይ አቶ ጌታቸው ረዳ " ዋጋ የማይጠይቅ የሠላም አማራጭ ሳለ በፖለቲከኞች የጠብ ርሃብ ምክንያት በርካታ ጉዳቶች ተከስተዋል " ብለዋል፡፡ "ልዩነቶች ቢኖሩ እንኳን ልዩነቶቹ ከአማራ እና ትግራይ ሕዝብ በታች ናቸው " ያሉ ሲሆን " አሁን የጦርነትን ምዕራፍ ዘግተን የሠላም አማራጮችን የምናይበት ጊዜ ነው " ሲሉም አክለዋል፡፡ "የሁከት እና ግርግር አጀንዳዎች የሚታያቸው ይኖራሉ፤ ነገር ግን ለሕዝብ ካሰብን እና ከሠራን ከሠላም ውጭ የተሻለ…
Read More
በትግራይ ክልል ከ3500 በላይ መምህራንና ተማሪዎች መገደላቸው ተገለጸ

በትግራይ ክልል ከ3500 በላይ መምህራንና ተማሪዎች መገደላቸው ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ለሁለት ዓመታት በዘለቀው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በትግራይ ክልል ስላደረሰው ውድመት ግንቦት መግለጫ ሰጥቷል፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የአስተዳደር በደል መከላከል ዳይሬክተር አዳነ በላይ በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ከ2ሺህ በላይ መምህራን እና ከ 1 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎች መገደላቸው ተረጋግጧል ብለዋል። ተቋሙ በሰጠው መግለጫ በትግራይ ክልል ብቻ 2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሰዎች የተፈናቀሉ ሲሆን በሁሉም የማበረሰብ ክፍል ላይ ጦርነቱ ውድመት ማድረሱ ተገልጿል። በዚሁ ጦርነት ምክንያት 88 በመቶ የመማሪያ ክፍሎች ሙሉ በሙሉ እና በከፊል ጉዳት ደርሶባቸዋል የተባለ ሲሆን 60 በመቶ የመማሪያ መፃሕፍት ደግሞ ከጥቅም ውጪ ሆነዋል ተብሏል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ የጦርነቱ ዳፋ መሠረተ ልማቶቹን በማውደም እና…
Read More