TPLF

75 ሺህ የትግራይ ተዋጊዎችን ወደ ቀድሞ ህይወታቸው ሊመለሱ ነው ተባለ

75 ሺህ የትግራይ ተዋጊዎችን ወደ ቀድሞ ህይወታቸው ሊመለሱ ነው ተባለ

የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን እንዳስታወቀው በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት ተሳትፎ ከነበራቸው 274 ሺህ የትግራይ ተዋጊዎችን ወደ ቀድሞ ህይወታቸው እንደሚመልስ አስታውቋል፡፡ ከዚህ ውስጥም በመጀመሪያው ምዕራፍ 75ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎችን ዲሞቢላይዝ የማድረግ ስራውን በነገው እለት በይፋ እንደሚጀመር ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡ ኮሚሽኑ ፕሮግራምና ፕሮጀክቶች በመቅረጽ ከሰባት ክልሎች ከ371 ሺህ በላይ የቀድሞ ተዋጊዎችን ከ760 ሚሊየን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ በሁለት ዓመታት ውስጥ የዲሞቢላይዜሽንና መልሶ ማቋቋም ስራውን ለመጨረስ የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጿል። ህዳር 12 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮም ለመጀመሪያው ዙር ተዋጊዎች ብተና ማስፈጸሚያ ሀብት መንግስትና ከለጋሾች ማግኘት ተችሏል ተብሏል፡፡ መንግስት ኮሚሽኑ ስራ ሲጀምር 1 ቢሊዮን ብር የተለገሰ ሲሆን በተጨማሪም ከ7 ሀገራት 60 ሚሊየን ዶላር መገኘቱ ተገልጿል። በድጋፍ የአውሮፓ…
Read More
በሀገር ክህደት ወንጀል የሞት ፍርድ ተወስኖባቸው የነበሩ 178 ወታደሮች በይቅርታ ተለቀቁ

በሀገር ክህደት ወንጀል የሞት ፍርድ ተወስኖባቸው የነበሩ 178 ወታደሮች በይቅርታ ተለቀቁ

ወታደሮቹ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት እና አመራሮች የነበሩ ሲሆን አዲስ አመትን አስመልክቶ ይቅርታ ተደርጎላቸዋል ከሶስት ዓመት በፊት ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በሀገር መከላከያ የሰሜን እዝ በህወሃት ታጣቂዎች መጠቃቱን ተከትሎ ነበር በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የተቀሰቀሰው፡፡ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ይህ ያልታሰበ ጥቃት እንዲደርስባቸው አቀነባብረዋል የተባሉ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት እና አመራሮች በሀገር ክህደት ወንጀል ተጠርጥረው ታስረው ነበር፡፡ እነዚህ 178 ወታደሮች በተመሰረተባቸው ክስ ጥፋተኛ ሆነው ተገኝተው የእድሜ ልክ እና ሞት ፍርድ ውሳኔ ተላልፎባቸው በእስር ላይ ነበሩ፡፡ በእስር ላይ የነበሩት የሠራዊት አባላቱ በፈፀሙት ወንጀል ተፀፅተው የይቅርታ ጥያቄአቸውን ለመንግስት እና ለመከላከያ ሚኒስቴር አሥገብተዋል ተብሏል። ወታደሮቹ የይቅርታ ጥያቄ ማስገባታቸውን ተከትሎ በአንድ በኩል ጉዳያቸው ለይቅርታ ቦርድ…
Read More
በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት ተጠያቂነት እንዲሰፍን ተጠየቀ

በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት ተጠያቂነት እንዲሰፍን ተጠየቀ

በሁለት አመቱ የትግራይ ጦርነት የተፈፀሙ ወንጀሎች ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ ዓረና ትግራይ ለሉአላዊነት እና ዴሞክራሲ ጥሪ አቀረበ። የያለፈው ጦርነት እና ጥፋት ተጠያቂነት ባለመረጋገጡ በጦርነቱ ተሳታፊ የነበሩ ሐይሎች ለሌላ ጥፋት እየተዘጋጁ ነው በማለት አረና ከሷል። በወቅታዊ የትግራይ ፖለቲካዊ ሁኔታ እና ሌሎች ጉዳዮች ዙርያ መግለጫ የሰጠው በትግራይ በተቃዋሚነት የሚንቀሳቀሰው ዓረና ትግራይ ለሉአላዊነት እና ዴሞክራሲ ህወሓት ውስጥ የተፈጠረው መከፋፈል ለትግራይ አደጋ ይዞ የሚመጣ እና ሐላፊነት የጎደለው አካሄድ እየተከተለ ያለ ሲል ገልፆታል። የዓረና ትግራይ ሊቀመንበር አቶ ዓምዶም ገብረስላሴ "አሁንም ወደ ጦርነት የሚወስዱ መንገዶች እየታዩ ያሉት እና የጦርነት ነጋሪት የሚጎሰመው ባለፈው 2 ዓመት ለነበረው ጦርነት ከሁሉም ወገን ተጠያቂነት ባለመረጋገጡ ነው፤ ከህወሓት ይሁን ከሻዕብያ እንዲሁም ብልፅግና ወገን የጦርነቱ…
Read More
ህወሃት ታጣቂዎቹ በሱዳን ጦርነት እየተሳተፉ ነው መባሉን አስተባበለ

ህወሃት ታጣቂዎቹ በሱዳን ጦርነት እየተሳተፉ ነው መባሉን አስተባበለ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ዛሬ ባወጣው መግለጫ "የህወሓት ኃይሎች" ከሱዳን ጦር ጎን በቅጥረኝነት ተሰልፈው ከሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ጋር እየተዋጉ ነው መባሉን አስተባብሏል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ ይህን ያለው የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች በትናትናው እለት ባወጣው መግለጫ የህወሓት ኃይሎች ከሱዳን ጦር እና ተባባሪ ሚሊሻዎች ጋር ሆነው እየተዋጉት እንደሆነ ማረጋገጡን መግለጹን ተከትሎ ነው። የሱዳን ጦርነት ከተጀመረበት ከሚያዝያ 2023 ወዲህ የሱዳን ጦር የውጭ ቅጥረኞችን እርዳታ እየፈለገ ነው የሚል ክስ ያቀረበው የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ጦር፣ በጦርነት ወቅት ተገድለው የተገኙ ቅጥረኞችን መመዝገቡን ጠቅሷል። የህወሓት ኃይሎች ከሱዳን ጦር ጎን ተሰልፈው  እየተዋጉ ነው የሚለውን የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች "መሰረተ ቢስ ክስ" በጽኑ እንደሚያወግዝ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ገልጿል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ እንደገለጸው ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች…
Read More
የአፍሪካ ህብረት በራያ እና አላማጣ የተከሰተው አዲስ ግጭት እንደሚያሳስበው ገለጸ

የአፍሪካ ህብረት በራያ እና አላማጣ የተከሰተው አዲስ ግጭት እንደሚያሳስበው ገለጸ

የአማራ እና የትግራይ ክልል የይገባኛል ጥያቄ በሚያነሱባቸው የራያ አላማጣ እና አካባቢዋ ግጭቶች መከሰታቸውን ተከትሎ የአፍሪካ ህብረት መግለጫ አውጥቷል። መግለጫው የህብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሀመት በአወዛጋቢዎቹ ራያ አላማጣ፣ ዛታ እና ኦፎላ "በአካባቢው ማህበረሰብ መካከል ያሉ ውጥረቶችን" በትኩረት እየተከታተሉት መሆኑን ገልጿል። በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በተደረሰው የፌደራል መንግስት እና የህወሓት የዘላቂ ሰላም ስምምነት፣ ሁለቱ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ የሚያነሱባቸው "አወዛጋቢ ቦታዎች" በህገመንግስቱ መሰረት እልባት እንዲያገኙ እንደሚደረግ ይጠቅሳል። ሊቀመንበሩ ሁለቱም ወገኖች ግጭት ከማባባስ እንዲታቀቡ እና የአካባቢውን ንጹሃን መፈናቀል እንዲያስቆሙ ጥሪ አቅርቧል። ከአፍሪካ ህብረት በተጨማሪም መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የሰባት ሀገራት ኤምባሲዎች በአማራ እና ትግራይ ከልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ ያጋጠመው አዲስ ግጭት እንዳሳሰባቸው አስታውቀዋል፡፡ የካናዳ፣…
Read More
ከአላማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ከ50 ሺህ አለፈ

ከአላማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ከ50 ሺህ አለፈ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት 50 ሺህ ዜጎች ከራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መፈናቀላቸውን አስታውቋል፡፡ እንደ ድርጅቱ ሪፖርት ከሆነ ከሰሞኑ በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ ባገረሸው ግጭት ምክንያት ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል ብሏል፡፡ ተፈናቃዮቹ በቆቦ፣ ወልደያ እና ሰቆጣ ከተሞች በሚገኙ መጠለያ ጣቢያዎች ላይ እንደተጠለሉም ድርጅቱ አስታውቋል፡፡ በአካባቢው ባለው አለመረጋጋት ምክንያት ተጨማሪ ዜጎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ የገለጸው ድርጅቱ ለተፈናቃዮች ውሃ፣ ምግብ እና ሌሎች ህይወት ማቆያ ድጋፍ በማድረግ ላይ መሆኑንም ገልጿል፡፡ አሁን ላይ ከለጋሽ ተቋማት እና ሀገራት የሚገኘው ድጋፍ እየተሟጠጠ በመሆኑ በአካባቢው ያለው ማህበረሰብ የሚችለውን ድጋፍ እያደረገ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ ለተፈናቃዮቹ መጠለያ፣ የሕክምና አገልግሎት እና ሌሎች መሰረታዊ ድጋፎችን ማድረግ ይገባል…
Read More
ከአላማጣ እና አካባቢው 29 ሺህ ህዝብ መፈናቀሉ ተገለጸ፡፡

ከአላማጣ እና አካባቢው 29 ሺህ ህዝብ መፈናቀሉ ተገለጸ፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት 29 ሺህ ዜጎች ከራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መፈናቀላቸውን አስታውቋል፡፡ እንደ ድርጅቱ ሪፖርት ከሆነ ከሰሞኑ በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ ባገረሸው ግጭት ምክንያት ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል ብሏል፡፡ ተፈናቃዮቹ በቆቦ፣ ሰሜን ወሎ እና ሰቆጣ ከተማ በሚገኙ መጠለያዎች ላይ እንደተጠለሉም ድርጅቱ አስታውቋል፡፡ በአካባቢው ባለው አለመረጋጋት ምክንያት ተጨማሪ ዜጎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ የገለጸው ድርጅቱ ለተፈናቃዮች ውሃ፣ ምግብ እና ሌሎች ህይወት ማቆያ ድጋፍ በማድረግ ላይ መሆኑንም ገልጿል፡፡ አሁን ላይ ከለጋሽ ተቋማት እና ሀገራት የሚገኘው ድጋፍ እየተሟጠጠ በመሆኑ በአካባቢው ያለው ማህበረሰብ የሚችለውን ድጋፍ እያደረገ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ ለተፈናቃዮቹ መጠለያ፣ የሕክምና አገልግሎት እና ሌሎች መሰረታዊ ድጋፎችን ማድረግ ይገባል…
Read More
አፍሪካ ህብረት በፕሪቶሪያ የተፈረመው የኢትዮጵያን የሰላም ስምምነት መገምገም ጀመረ

አፍሪካ ህብረት በፕሪቶሪያ የተፈረመው የኢትዮጵያን የሰላም ስምምነት መገምገም ጀመረ

በዚህ ግምገማ መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት፣ ህወሃት፣ በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሀመር እና ሌሎችም ተገኝተዋል፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ ለሁለት ዓመታት በዘለቀው ጦርነት የአፍሪካ ህብረት በደቡብ አፍሪካ ዋና ከተማ ፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ጦርነቱ መቆሙ ይታወሳል፡፡ ይህ የሰላም ስምምነት ከተፈረመ አንድ ዓመት ያለፈው ሲሆን በስምምነቱ መሰረት ያልተፈጸሙ ጉዳዮች እንዳሉ በሁለቱም ወገኖች ሲነሳ ቆይቷል፡፡ አፍሪካ ህብረት በኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት መካከል የተደረሰውን የፕሪቶሪያ የተኩስ ማቆም ስምምነት አፈፃፀም ስትራቴጂካዊ ግምገማ እያካሄደ መሆኑን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ይፋ አድርገዋል። የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ በኤክስ ገፃቸው ባጋሩት መልእክት የአፍሪካ ህብረት በኢትዮጵያ መንግስት እና በህዝባዊ ወያነ ሓርነት…
Read More
ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ከአራት ዓመት በኋላ ወደ አዲስ አበባ መጡ

ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ከአራት ዓመት በኋላ ወደ አዲስ አበባ መጡ

የትግራይ ክልል የቀድሞ ፕሬዝዳንት ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ከአራት ዓመት በኋላ ወደ አዲስ አበባ መጡ:: ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ኢትዮጵያ ለዓመታት ወደ ጦርነት እንድተገባ የተገደደችበትን የሀገር መከላከያ ሰራዊት ሰሜን እዝ እሳቸው የሚመሩት የትግራይ ልዩ ሀይል እንዲያጠቃ ማድረጋቸው አይዘነጋም፡፡ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን የተገደሉበት እና 28 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ ንብረት የወደመበት ይህ ጦርነት ከአንድ ዓመት በፊት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ቆሟል፡፡ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በዛሬው ዕለት ከአራት ዓመት በኋላ ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ የመጡ ሲሆን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር ፊት ለፊት ተገናኝተዋል፡፡ ደብረጽዮን እና ሌሎች የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ኃላፊዎች ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ጋር በአዲስ አበባ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም…
Read More
ጦርነት እና እግር ኳስ በኢትዮጵያ….

ጦርነት እና እግር ኳስ በኢትዮጵያ….

ቢኒያም ተክለወይኒ እባላለሁ። ትውልዴ ሽረ ነው። ከጦርነቱ በፊት የፕሪሚየር ሊጉ ተካፋይ የሆነው የስሑል ሽረ ዋና ቡድን ተጨዋች ነበርኩ ። ሊብሮ ነኝ ። አሰልጣኝ ዳንኤል ፀሐዬ ዋና አሰልጣኛችን ነበር ። ኳስ እወዳለሁ ። ደጉ ደበበን አደንቃለሁ ። እንደ እርሱ የመሆን ምኞት ነበረኝ ። ተቀራኒ ሆነን ተጫውተናልም:: በኳስ ጨዋታ መከላከልን እወዳለሁ ። አዳነ ሳላ አማኑኤልን ጨምሮ ከብዙ ጎበዝ አጥቂዎች ተፋጥጫለሁ ። ሁሉንም ገትሬ አቁሜያለሁ ። ቡድኔ ጎል እንዳይቆጠርበት በአግባቡ መምራት መከላከል ከስሑል ሽረ ጋር በፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን መሆን የዘወትር ህልሜ ነበር ። ከሽረ ውጭ ሌላ ክለብ አላውቅም ። በኳስ ጨዋታ መንገዴ የእራሴንም የቤተሰቦቼንም ህይወት መቀየር ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተመርጦ መጫወት የሌት ተቀን…
Read More