24
Jan
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ጋምቤላ ክልሎች ያደረጋቸውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርት ይፋ አድርጓል፡፡ ኮሚሽኑ እንደለጸው ሪፖርቱ ከመስከረም ወር አጋማሽ 2017 ዓ.ም እስከ ታኅሣሥ 2017 ዓ.ም አጋማሽ ባለው ጊዜ ውስጥ ያለውን ጊዜ የሚመለከት ነው ብሏል፡፡ ሪፖርቱ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ በግጭት ዐውድ ውስጥ ባሉ አካባቢዎች የተፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን በሙሉ የሚሸፍን አይደለም ያለው ኮሚሽኑ በእነዚህ አካባቢዎች በነጻነት ተንቀሳቅሶ የተሟላ ክትትልና ምርመራ ለማካሄድ ምቹ ሁኔታ ባለመኖሩ፣ ውጤታማ ክትትልና ምርመራ የተከናወነባቸውን ጉዳዮች ብቻ በማሳያነት እንዳቀረበም ገልጿል፡፡ ኢሰመኮ በሪፖርቱ ላይ እንደጠቀሰው በግጭት በተጎዱ አካባቢዎች ከደረሱ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች አሳሳቢ ሆነው ከቀጠሉ ጉዳዮች መካከልም ከፍርድ ውጭ ግድያ መፈጸም፣ በግጭት ዐውድና አካባቢ የሚደርስ የሲቪል…