IDPs

ከአላማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ከ50 ሺህ አለፈ

ከአላማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ከ50 ሺህ አለፈ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት 50 ሺህ ዜጎች ከራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መፈናቀላቸውን አስታውቋል፡፡ እንደ ድርጅቱ ሪፖርት ከሆነ ከሰሞኑ በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ ባገረሸው ግጭት ምክንያት ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል ብሏል፡፡ ተፈናቃዮቹ በቆቦ፣ ወልደያ እና ሰቆጣ ከተሞች በሚገኙ መጠለያ ጣቢያዎች ላይ እንደተጠለሉም ድርጅቱ አስታውቋል፡፡ በአካባቢው ባለው አለመረጋጋት ምክንያት ተጨማሪ ዜጎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ የገለጸው ድርጅቱ ለተፈናቃዮች ውሃ፣ ምግብ እና ሌሎች ህይወት ማቆያ ድጋፍ በማድረግ ላይ መሆኑንም ገልጿል፡፡ አሁን ላይ ከለጋሽ ተቋማት እና ሀገራት የሚገኘው ድጋፍ እየተሟጠጠ በመሆኑ በአካባቢው ያለው ማህበረሰብ የሚችለውን ድጋፍ እያደረገ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ ለተፈናቃዮቹ መጠለያ፣ የሕክምና አገልግሎት እና ሌሎች መሰረታዊ ድጋፎችን ማድረግ ይገባል…
Read More
ኢትዮጵያ ለተረጂዎች ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልጋት ገለጸች

ኢትዮጵያ ለተረጂዎች ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልጋት ገለጸች

በኢትዮጵያ እያሻቀበ ላለው የተረጂዎች ቁጥር ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ እንደሚያስፈልግ መንግስት አስታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ በተለያዩ ምክንያቶች ለተፈናቀሉ ዜጎች የምግብ ርዳታ ለማቅረብ 3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና የኢትዮጵያ መንግሥት በጋራ ባወጡት ሪፖርት ላይ አስታውቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ከፍተኛ የሕዝብ ግንኙነት ባለሞያ አቶ አታለለ አቡሃይ፣ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ያለው የተረጅዎች ብዛት 6 ነጥብ6 ሚሊዮን መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የተፈጥሮ አደጋዎች፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ ጦርነት እና ሌሎች አደጋዎች ምክንያት የተፈናቃዮች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ተገልጿል፡፡ የብሪታንያ የአፍሪካ ልማት ዳይሬክተር በኢትዮጵያ ለሁለት ቀናት ጉብኝት ካደረጉ በኋላ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች የ125 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ዳይሬክተሩ አክለውም አሳሳቢ የምግብ…
Read More
የጸጋ ተስፋዎች እና በህይወት የመኖር ትግል

የጸጋ ተስፋዎች እና በህይወት የመኖር ትግል

ጸጋ ትባላለች በትግራይ ክልል ደንጎላት በተባለ አካባቢ የተወለደች ሲሆን እድገቷም ሆነ የትዳር ሕይወቷን በዚያው ያደረገች ወጣት እናት ናት። ጸጋ ወደ ትዳር ስትገባ የ16 ዓመት ታዳጊ ነበረች በወቅቱ በቤተሰብ ስምምነት በተፈጸመው በዚህ ትዳር 2 ሴት እና 2 ወንድ በአጣቃላይ 4 ልጆችን አፍርተውበታል። በወቅቱ በነበሩበት አካባቢ በቆሎ በማምረት እና በመሸጥ ከባለቤቷ ጋር ጥሩ ኑሮ ይኖሩ የነበሩ ሰዎችም ነበሩ። ነገር ግን ይህ ጥሩ የሚባለው ኑሮ በጥቂት ጊዜያት ውስጥ የተገላቢጦች እየሆነ መጣ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተፈጠረው ጦርነት ነገሮች መስመራቸውን እየለቀቁ መጡ... በወቅቱ የንግድ እንቅስቃሴዎች እየቀነሱ መምጣታቸው መሠረታዊ የሚባሉ ነገሮች በተለይም ምግብ ነክ ሸቀጦች ዋጋቸው የማይቀመስ ሆነ እንደ ቡና፣ ጨው፣ ስኳር እና መሰል ነገሮችን ማግኘት…
Read More
በኢትዮጵያ ከ4 ሚሊዮን በላይ ዜጎች መፈናቀላቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ ከ4 ሚሊዮን በላይ ዜጎች መፈናቀላቸው ተገለጸ

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ተቋም (IOM) ከባለፈው ሕዳር እስከ ሰኔ ወር ድረስ በ3 ሺሕ 300 መጠለያ ጣቢያዎች ሰበሰብኩት ባለው መረጃ፤ በኢትዮጵያ ከ11 ክልሎች ከ4 ነጥብ 38 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ተፈናቅለዋል ብሏል፡፡ ከነዚህ ተፈናቃዮች 66 በመቶ የሚሆኑት በግጭት ምክንያት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን ቀሪዎቹ በድርቅ እና በማህበራዊ ችግሮች ምክንያት መፈናቀላቸው ተገልጿል፡፡ሶማሌ ክልል በድርቅ ምክንያት የተፈናቀሉ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች መገኛ መሆኑ ሲገለጽ፤ ትግራይ፣ አማራ ፣ኦሮሚያ እና አፋር ክልሎች በግጭት የተፈናቀሉ ዜጎች ያሉባቸው አካባቢዎች ናቸው ተብሏል፡፡ በተመሳሳይ በ10 ክልሎች ተፈናቃዮችን ለመመለስ በተደረገ ጥናት 3 ነጥብ 24 ሚሊዮን ተፈናቃዮች ወደ ቦታቸው መመለስ ይችላሉ በሚል መለየታቸውም ተገልጿል፡፡ተቋሙ አክሎም በአገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተፈናቃዮች የተመለሱባቸው…
Read More
አሜሪካ በኢትዮጵያ ለሰብዓዊ ድጋፍ የሚውል 331 ሚሊዮን ዶላር ለገሰች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ለሰብዓዊ ድጋፍ የሚውል 331 ሚሊዮን ዶላር ለገሰች

አሜሪካ ለኢትዮጵያ ከ331 ሚሊየን ዶላር በላይ የሰብአዊ ድጋፍ ይፋ አደረገች። ለሥራ ጉብኝ አዲስ አበባ የሚገኙት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ለኢትዮጵያ ከ331 ሚሊየን ዶላር በላይ የሰብአዊ ድጋፍ ይፋ አድርገዋል። አንቶኒ ብሊንከን እንዳስታወቁት ድጋፉ በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት እና በአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት አማካኝነት የሚሸፈን ነው፡፡ ድጋፉም በተለያዩ ምክንያቶች በችግር ለተጋለጡ ወገኖች ለምግብ፣ ለመድሃኒት፣ ለንጹህ የመጠጥ ውሃ የሚውል መሆኑን ገልፀዋል። ይህም በግጭት ለተጎዱ፣ ለተፈናቀሉ፣ በድርቅ ለተጠቁ እና ለምግብ እጥረት ለተጋለጡ ዜጎች ሕይወት አድን ድጋፍ ማድረግ ያስችላል ተብላል።
Read More