Teachers

18 የዶክትሬት ድግሪ ዩንቨርሲቲ መምህራን ደብዛቸው እንደጠፋ ተገለጸ፡፡

18 የዶክትሬት ድግሪ ዩንቨርሲቲ መምህራን ደብዛቸው እንደጠፋ ተገለጸ፡፡

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የኦዲት ግኝት ሪፖርት ላይ መክሯል፡፡ የቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር እና የዩንቨርሲቲው አመራር አባላት በጋራ ባደረጉት ውይይት ላይ እንደተገለጸው ለሶስተኛ ድግሪ በሚል ለትምህርት የተላኩ እና የጠፉ የዩንቨርሲቲው መምህራን ጉዳይ ዋነኛው ነው፡፡ የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ እና የፌደራል ዋና ኦዲተር አመራሮች ዩንቨርሲቲው ለሶስተኛ ድግሪ ትምህርት ብሎ ስፖንሰር ሆኖ የላካቸው መምህራን በወቅቱ ትምህርታቸውን አጠናቀው እንዳልተመለሱ፣ ዩንቨርሲቲውም ለነዚህ መምህራን የከፈለውን ከ7 ሚሊዮን በላይ ብር ገንዘብ ለምን ተመላሽ አላደረክም? በሚል ጥያቄ አንስተዋል፡፡ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ደረጀ እንግዳ (ዶ/ር) ከ2011 ዓ.ም…
Read More
በትግራይ ክልል ከ3500 በላይ መምህራንና ተማሪዎች መገደላቸው ተገለጸ

በትግራይ ክልል ከ3500 በላይ መምህራንና ተማሪዎች መገደላቸው ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ለሁለት ዓመታት በዘለቀው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በትግራይ ክልል ስላደረሰው ውድመት ግንቦት መግለጫ ሰጥቷል፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የአስተዳደር በደል መከላከል ዳይሬክተር አዳነ በላይ በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ከ2ሺህ በላይ መምህራን እና ከ 1 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎች መገደላቸው ተረጋግጧል ብለዋል። ተቋሙ በሰጠው መግለጫ በትግራይ ክልል ብቻ 2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሰዎች የተፈናቀሉ ሲሆን በሁሉም የማበረሰብ ክፍል ላይ ጦርነቱ ውድመት ማድረሱ ተገልጿል። በዚሁ ጦርነት ምክንያት 88 በመቶ የመማሪያ ክፍሎች ሙሉ በሙሉ እና በከፊል ጉዳት ደርሶባቸዋል የተባለ ሲሆን 60 በመቶ የመማሪያ መፃሕፍት ደግሞ ከጥቅም ውጪ ሆነዋል ተብሏል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ የጦርነቱ ዳፋ መሠረተ ልማቶቹን በማውደም እና…
Read More