12
Aug
ቢኒያም ተክለወይኒ እባላለሁ። ትውልዴ ሽረ ነው። ከጦርነቱ በፊት የፕሪሚየር ሊጉ ተካፋይ የሆነው የስሑል ሽረ ዋና ቡድን ተጨዋች ነበርኩ ። ሊብሮ ነኝ ። አሰልጣኝ ዳንኤል ፀሐዬ ዋና አሰልጣኛችን ነበር ። ኳስ እወዳለሁ ። ደጉ ደበበን አደንቃለሁ ። እንደ እርሱ የመሆን ምኞት ነበረኝ ። ተቀራኒ ሆነን ተጫውተናልም:: በኳስ ጨዋታ መከላከልን እወዳለሁ ። አዳነ ሳላ አማኑኤልን ጨምሮ ከብዙ ጎበዝ አጥቂዎች ተፋጥጫለሁ ። ሁሉንም ገትሬ አቁሜያለሁ ። ቡድኔ ጎል እንዳይቆጠርበት በአግባቡ መምራት መከላከል ከስሑል ሽረ ጋር በፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን መሆን የዘወትር ህልሜ ነበር ። ከሽረ ውጭ ሌላ ክለብ አላውቅም ። በኳስ ጨዋታ መንገዴ የእራሴንም የቤተሰቦቼንም ህይወት መቀየር ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተመርጦ መጫወት የሌት ተቀን…