Mekelle

በትግራይ ታጣቂዎች መካከል ያለው ውጥረት እንዳሳሰባቸው ነዋሪዎች ተናገሩ

በትግራይ ታጣቂዎች መካከል ያለው ውጥረት እንዳሳሰባቸው ነዋሪዎች ተናገሩ

በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ባለፉት ሶስት ቀናት የተፈጠሩ አለመረጋጋቶች ነዋሪዎችን እንዳስጨነቃቸው ተናግረዋል፡፡ ያነጋገርናቸው የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች እንዳሉት የትግራይ ታጣቂዎች ከነ ትጥቃቸው ወደ ከተማዋ በመግባት ሲንቀሳቀሱ የታዩ ሲሆን በተለይም የክልሉ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት አካባቢ ያለው ሁኔታ አስፈሪ ነው ብለዋል፡፡ ለደህንነቱ በመስጋት ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ ነዋሪ እንዳለው ከሆነ "ከዚህ ቀደምም ብዙ አስተያየት ሰጥተናል፤ ሰሚ ግን የለም። ህዝቡ ጦርነት ሰልችቶናል ፤ እስካሁን ያደረጋችሁት የእርስ በርስ ግጭት ይበቃችኋል ብሏል። ገላጋይ ነው ያጣነው " ብለዋል። ከትናንት በስቲያ ጀምሮ የደመወዝ ይከፈለን የሚሉ ጥያቄዎችን ይዘው ወደ ከተማዋ ገብተዋል የተባሉት ታጣቂዎች ላለፉት ሁለት ቀናት የፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤትን እንደከበቡ ናቸውም ተብሏል፡፡ ታጣቂዎቹ ከከልሉ ፕሬዝዳንት ጸህፈት ቤት በተጨማሪም የክልሉ መንግስት…
Read More
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፌደራል መንግስትን እገዛ ጠየቀ

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፌደራል መንግስትን እገዛ ጠየቀ

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በክልሉ ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ነው የፌደራል መንግስትን እገዛ የጠየቀው። ጊዜያዊ አስተዳደሩ በመግለጫው “ከጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ አንዳንድ የትግራይ ሰራዊት ከፍተኛ አዛዦች ከተልኮ ወጭ የአንድ ጠባብ ቡድን የስልጣን ጥም ለማርካት በማለት ግልፅ የመፈንቅለ መንግስት እንስቃሴ ሲያደርጉ ቆይተዋል” ብሏል። “በዚህ ሳምንትም በተመሳሳይ በሰሜን ምስራቅና በደቡብ ግንባር አዛዦች እንቅስቃሴው በከፋ ሁኔታ ተባብሶ ቀጥሏል” ብሏል መግለጫው። ይህንን አደገኛ እንቅስቃሴ ለመግታት እና ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ሁሉ ለማስቆም የካቲት 26 ቀን 2017 ዓ.ም ለትግራይ ጦር ዋና አዛዥ ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ ትእዛዝ ቢሰጥም ማስቆም እንዳልቻለ አስታውቋል። ሁኔታው እልባት ባለማግኘቱ የግንባሩ የጦር አዛዦች  እገዳ እንደተጣለባቸው ያመላከተው መግለጫው፤ የጸጥታ ቢሮ…
Read More
በጦርነት በተጎዳችው ትግራይ የ6 ቢሊዮን ብር ብረት ማምረቻ ፋብሪካ ሊገነባ እንደሆነ ተገለጸ

በጦርነት በተጎዳችው ትግራይ የ6 ቢሊዮን ብር ብረት ማምረቻ ፋብሪካ ሊገነባ እንደሆነ ተገለጸ

በ6 ቢሊዮን ብር ወጪ በኢትዮጵያ እና ቻይና ባለሃብቶች ትብብር የብረታ-ብረት ማምረቻ ኢንዱስትሪ በመቐሌ ከተማ ሊገነባ ነው። በአስር ወራት ውስጥ የሚገነባው ይህ ኢንዱስትሪ የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ዛሬ ይፋ ተደርጓል። በዚህ ወቅት የትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ፤ የሌጀንድ ብረታብረት ኢንዱስትሪ ሃላፈነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል የሚፈጥር በመሆኑ አስፈጊው ድጋፍ ይደረግለታል ብለዋል። ሌሎች በግልና በማህበር የተደራጁ ባለሃብቶችም የዚህን የልማት ፕሮጀክት አርአያ ተከትለው በማልማት  ራሳቸውንና ሀገራቸውን እንዲጠቅሙ መልእክት አስተላልፈዋል። የብረታብረት ማምረቻው 75 በመቶ በኢትዮጵያዊው ባለሃብት ኢንጅነር ያሬድ ተስፋይ የተሸፈነ ሲሆን ቀሪው 25 በመቶ ደግሞ በቻይናዊው ባለሃብት ሚስተር ሊ ዮን መሸፈኑን የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ሳምሶም ገብረመድህን ገልጸዋል።…
Read More