redsea

ኬንያ ለኡጋንዳ የባህር በር እንደምትሰጥ አስታወቀች

ኬንያ ለኡጋንዳ የባህር በር እንደምትሰጥ አስታወቀች

ከአንድ ሳምንት በፊት የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ዮሪ ሙሴቪኒ ሀገራቸው የባህር በር ካላገኘች ከኬንያ ጋር ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል ሲሉ ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል። ኬንያ ለኡጋንዳ ጥያቄ በይፋ መልካም ምላሽ ሰጥታለች። የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ጎረቤቷ ለሆነችው ኡጋንዳ የባሕር በር እንደምትሠጥ አስታውቀዋል። ኡጋንዳ በኬንያ በኩል በነዳጅ ቧንቧ፣ በመንገድ እና በባቡር ሐዲድ አማካኝነት በሕንድ ውቅያኖስ ላይ የባሕር በር እንድታገኝ እናደርጋለን ብለዋል ፕሬዝዳንት ሩቶ። ኬንያ ለኡጋንዳ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ሲባል የነዳጅ ማስተላለፊያ ቧንቧዋን የሚያስተዳድረውን መንግሥታዊ ኩባንያ ከኡጋንዳ ጋር በጋራ ባለቤትነት ለመያዝ ፍቃደኛ መኾኗንም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል። ኬንያ በቻይና እርዳታ የተዘረጋውን የባቡር ሐዲዷን በቅርቡ እስከ ኡጋንዳ መዲና ካምፓላ ከተማ ድረስ እንደምትዘጋም በፕሬዝዳንቷ በኩል አስታውቃለች። ሌላኛዋ ወደብ አልባ ሀገር ኢትዮጵያ…
Read More
ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችው በህወሀት ምክንያት መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ተናገሩ

ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችው በህወሀት ምክንያት መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ተናገሩ

የሀገር መከላከያ ሰራዊት አዛዥ ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሰሜን እዝ ላይ የተፈጸመውን ጥቃት ለማሰብ በሚል በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ህወሀትን ተችተዋል። ፊልድ ማርሻል በዚህ ጊዜ እንዳሉት መከላከያ ሠራዊት ሕይወቱን ከሰጠለት ሕዝብ ውስጥ የወጡ ጥቂት ካሃዲዎች ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ከኋላው መውጋታቸው ሕመሙ ጥልቅ ነው ብለዋል። በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈፀመው ክህደት ወንድም ወንዱሙ ላይ የፈፀመው ክህደት በመሆኑ በታሪክ ልዩ እንደሚያደርገውም ጠቅሰዋል። የትግራይ ሕዝብ በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመውን ክህደት አይቀበለውም ያሉት አዛዡ  የትግራይ ሕዝብ በልጆቹ ክህደት አፍሮ፣ ተመልሰን መቐለ ስንገባ አጨብጭቦ ተቀብሎን ነበር ሲሉም አክለዋል። ስለዚህ ክህደት እና አስነዋሪ ታሪክ ስናውራ ስለ ጥቂት የሕወሓት አመራሮች እንጂ ስለ ትግራይ ሕዝብ እንዳልሆነም ገልጸዋል። የህወሀት…
Read More
ኢትዮጵያ የአሰብ ወደብን ከኤርትራ መረከቧ አይቀሬ መሆኑን ገለጸች

ኢትዮጵያ የአሰብ ወደብን ከኤርትራ መረከቧ አይቀሬ መሆኑን ገለጸች

የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ምክትል አዛዥ ኮሞዶር ተገኝ ለታ እንዳሉት የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ሰላምና መረጋጋት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። ምክትል አዛዡ ይህን የተናገሩት ጥቅምት 8 ቀን 2018 ዓ.ም በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በመከላከያ ዋር ኮሌጅና በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ትብብር “የሁለቱ የውሃ ሥርዓቶችና የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ነፃነት፣ የዓባይና የቀይ ባሕር ትስስር እና የአፋር ክልልን ስትራቴጂካዊ ሚና መዳሰስ” በሚል ርዕስ በሠመራ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደ የምክክር መድረክ ላይ ነው። በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ምክትል አዛዥ ኮሞዶር ተገኝ ለታ የኢትዮጵያ ወደብ አልባ መሆን በሀገሪቱ ላይ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ቀንድ ሊኖረው የሚችለው ኢኮኖሚዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ወታደራዊ መዘዝን መረዳት ተገቢ መሆኑንም አጽኖት ሰጥተው…
Read More
ኢትዮጵያ ከየትኛውም ወገን የሚሰነዘርባትን ጥቃት ለመመከት ጦሯ ዝግጁ መሆኑን ገለጸች

ኢትዮጵያ ከየትኛውም ወገን የሚሰነዘርባትን ጥቃት ለመመከት ጦሯ ዝግጁ መሆኑን ገለጸች

የሀገር መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፎልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እንዳሉት ሰራዊቱ “ከየትኛውም አቅጣጫ የሚሰነዘርበትን ጥቃት” ለመመከት ዝግጁ ነው ብለዋል፡፡ ዋና አዛዡ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ በሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ለ24ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን መኮንኖች ባስመረቀበት ወቅት እንዳሉት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ወቅት “በሰላማዊ መንገድ የባህር በር ለማግኘት ጥረት እያደረገች ያለችበት ነው” ያሉት አዛዡ የሀገሪቱ ታሪካዊ ጠላቶች የውስጥ ችግሮችን ለማባባስ “የቋመጡበት እና የቆረጡበት” ወቅት እንደሆነም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ “ከቀይ ባህር ተገፍታ በመቆየቷ የደረሰባትን የኢኮኖሚና የጸጥታ ተግዳሮቶችን እና ስብራቶችን” ለመቅረፍ “እየሞከረች” ያለችበት መሆኑን ልብ ሊሉት እንደሚገባ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ለተመራቂ ወታደራዊ መኮንኖቹ አሳስበዋል። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ…
Read More
የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ጉዳይ ሊሰበሰብ ነው

የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ጉዳይ ሊሰበሰብ ነው

የተባበሩት መንግስታ ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በኢትዮጵያና ሶማሊያ ጉዳይ ላይ ሊሰበሰብ መሆኑን አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና የራስ ገዟ ሶማሊላንድ ፕሬዝደንት ሙሴ ቢሄ አብዲ ከአንድ ወር በፊት በአዲስ አበባ የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸው ይታወሳል። ስምምነቱን ተከትሎም ሶማሊላንድ የግዛቴ አንድ አካል ናት የምትለው ሶማሊያ የዲፕሎማሲ የበላይነት ለማግኘት የተለያዩ ጥረቶችን በማድረግ ላይ ትገኛለች። በዚሁ መሰረት ሶማሊያ ባለፈው ሳምንት  ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር ያደረገችው ስምምነት የተመድን ቻርተር ጥሷል በሚል ምክር ቤቱ ስብሰባ እንዲቀመጥ እና እንዲወያይበት አመልክታም ነበር። ይህንን ተከትሎም የጸጥታው ምክር ቤት የወሩ ፕሬዝዳንት ፈረንሳይ በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ ጉዳይ ላይ በአፍሪካ ሰላምና ደህንነት አጀንዳ ስር ለመምከር ስብሰባ መጥራቷ ታውቋል። የጸጥታው ምክር ቤት በዛሬው…
Read More
አሜሪካ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ እንደሚሰጋት ገለጸች

አሜሪካ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ እንደሚሰጋት ገለጸች

የአሜሪካ የታችኛው ምክር ቤት ኮንግረስ የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ የአፍሪካ ጉዳዮች ንኡስ ኮሚቴ፣  ‘”በኢትዮጵያ ተስፋ ወይንስ ስጋት፣ የአሜሪካ ፖሊሲ ሁኔታ’’ ላይ ትላንት ምሸት ምስክርነት ሰምቷል፡፡ የኮሚቴው አባላት ለአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር፣ ስለ ባህር በር በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ስለተነሳው ጥያቄ የአሜሪካን አቋም ጠይቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ “የወደብ ጉዳይ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ ነው” ብለው መናገራቸው በቀጠናው ካሉ አገራት አልፎ ለአሜሪካ ስጋት እንደሆነ ማይክ ሐመር ተናግረዋል። ይሁን እንጂ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የባህር በር ፍላጎት በኃይል ተፈጻሚ እንደማይሆን በይፋ እንዲሁም በግል ማረጋገጫ እንደሰጧቸው አመልክተዋል። ጥያቄው በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ስጋት እንደፈጠረ የጠቆሙት ማይክ ሐመር፣ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ የሚቀጠል ከሆነ…
Read More
የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ስለባህር በር አስተያየት ሲሰጡ እንዲጠነቀቁ ተጠየቀ

የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ስለባህር በር አስተያየት ሲሰጡ እንዲጠነቀቁ ተጠየቀ

ባለስልጣናት ስለ ባህር በር ጉዳይ የሚሰጡት መግለጫ የተጠናና ጥንቃቄ የተሞላበት መሆን እንዳለበት ምሁራን አሳስበዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ የባህር በር ዙሪያ የምሁራን ውይይት መድረክ አዘጋጅቶ ነበር፡፡ በዚህ የምሁራን መድረክ ላይ ጥናት ያቀረቡና ውይይት ያደረጉ ምሁራን፣ መንግሥት ስለባህር በር የሚሰጣቸው መረጃዎች የጎረቤት አገሮችን የማያሠጉና ጥንቃቄ የተሞላባቸው እንዲሆኑ አሳስበዋል፡፡ ‹‹ፍትሐዊ የወደብ አጠቃቀም ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና ልማት›› በሚል ርዕስ በተስተናገደው በዚህ ዓውደ ጥናት ላይ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ የባህር በር ባለቤት መሆን ስለምትችልባቸው አማራጮች ሰፊ ምሁራዊ ውይይት ተካሂዷል፡፡ በጥናት መድረኩ ላይ ለኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄን በማስመለስ ታሪካዊ ድል ያስመዘገቡ ያለፈው ትውልድ ምርጥ ተሞክሮ ታሪካዊ ድል እንደነበር ተገልጿል፡፡ በሰላማዊ መንገድ ኤርትራን በፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ ጋር…
Read More