EU

የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ የ32 ቢሊዮን ብር ገንዘብ ድጋፍ አደረገ

የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ የ32 ቢሊዮን ብር ገንዘብ ድጋፍ አደረገ

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ተፈናቃዮችን መልሶ ማቋቋምን ጨምሮ ለስድሰት የልማት ፕሮጀክቶች የሚውል የ32 ቢሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡ ኢትዮጵያና የአውሮፓ ህብረት ለስድሰት ዋና ዋና የልማት ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ የሚውል የ240 ሚሊየን ዩሮ ወይም የ32.3 ቢሊየን ብር የልማት ድጋፍ ስምምነት በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል። ከፕሮጀክቶቹ መካከል በግጭት የተጎዱ አካባቢዎችን አስተዳደርና አካታችነትን በማሻሻል መረጋጋትን ማስፈን የሚለው ይገኝበታል። በተጨማሪም በግጭት የተጉዱ የጤና ተቋማትን ወደ አገልግሎት ለመመለስና እንዲሁም ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ በማቋቋም ላይ ትኩረት ያደርጋል ተብሏል፡፡ የስራ ዕድል የሚፈጥሩ የግብርና ስራዎችን፣ የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን በመጠቀም የዜጎችን የዲጂታል ክህሎት ልማትን በማሳደግ የኢኮኖሚ ዕድገትን ማምጣት፣ የዴሞክራሲ ተቋማትን ማጠናከር ደግሞ ሌሎቹ የድጋፍ ስምምነቱ ፕሮጀክቶች አካል መሆናቸው ተጠቁሟል። በፊርማ ስነ…
Read More
አሜሪካንን ጨምሮ ከ25 በላይ ሀገራት በትግራይ ያለው አለመረጋጋት አሳስቦናል አሉ

አሜሪካንን ጨምሮ ከ25 በላይ ሀገራት በትግራይ ያለው አለመረጋጋት አሳስቦናል አሉ

በትግራይ ክልል በጊዜያዊ አስተዳድሩ እና በእነ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ቡድን መካከል ግጭት መከሰቱን ተከትሎ የመፈንቅለ መንግስት እየተፈጸመ መሆኑን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳድር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ መናገራቸው ይታወሳል፡፡ አቶ ጌታቸው ረዳ በመቀሌ እና አዲ አበባ በሰጧቸው መግለጫዎች ላይ እንዳሉት የህወሃት አንዱ ክንፍ በጊዜያዊ አስተዳድሩ ላይ አመራሮችን መሾም፣ ማህተም መቀማት፣ ቢሮዎችን መቆጣጠር እና ሌሎች ህጋዊ ያልሆኑ ስራዎችን እያካሄደ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ይህን ተከትሎ በትግራይ ክልል አለመረጋጋት የተፈጠረ ሲሆን በክልሉ ዳግም ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል የሚሉ ስጋቶች አይለዋል፡፡ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ ከ20 በላይ ሀገራትም በትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ እንዳሳሰባቸው ባወጡት የጋራ መግለጫ ላይ ገልጸዋል፡፡ የጋራ መግለጫውን ካወጡ ሀገራት መካከል አሜሪካ፣ ብሪታንያ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ጀርመን፣ፈረንሳይ፣ ስዊድን፣ ቤልጂየም እና…
Read More
አዲሱ የአውሮፓ ህብረት ሕግ በአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ገበሬዎች ላይ የሕልውና አደጋ ደቅኗል ተባለ

አዲሱ የአውሮፓ ህብረት ሕግ በአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ገበሬዎች ላይ የሕልውና አደጋ ደቅኗል ተባለ

የአውሮፓ ህብረት ከሁለት ሳምንት በፊት ባወጣው አዲስ ህግ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን የሚጎዱ ምርቶችን ወደ ህብረቱ አባል ሀገራት ገበያዎች እንዳይገቡ እና እንዳይሸጡ አደርጋለሁ ብሏል፡፡ የምድርን ሙቀት ለመከላከል እና የደን ምንጣሮን ለመከላከል ይረዳል በሚል የተዘጋጀው ይህ ህግ ከደን ምርቶች ጋር የተያያዙ ምርቶች በአውሮፓ የገበያ እድል እንዳያገኙ መከልከል እና የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን ማበረታታት የህጉ ዋነኛ ዓላማ ነው፡፡ ይህ ሕግ የጫካ ቡናዎችን ወደ አውሮፓ እና ሌሎች ዓለም ገበያ መዳረሻዎች የምትልከው ኢትዮጵያን እንደሚመለከት ስጋቶች ተነስተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ቡና ማህበር ጉዳዩ እንዳሳሰበው ገልጾ አዲሱ የአውሮፓ ህግ የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ እንዲረዳ ካልተደረገ ሚሊዮኖች ወደ ድህነት ሊወርዱ ይችላሉ ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡ የማህበሩ ፕሬዝዳንት ሁሴን አምቦ (ዶ/ር) ለአልዐይን እንዳሉት “በኢትዮጵያ ቡና…
Read More