Humanrightsviolations

መንግሥት የጎዳና ተዳዳሪዎችን በግዴታ ወደ ማጎሪያ ስፍራ እያስገባ መሆኑን ኢሰመኮ ገለጸ

መንግሥት የጎዳና ተዳዳሪዎችን በግዴታ ወደ ማጎሪያ ስፍራ እያስገባ መሆኑን ኢሰመኮ ገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በጎዳና ላይ ያሉ ሰዎችን ያለፈቃዳቸው መያዝና ወደ ማቆያ ማዕከላት ማስገባት የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን ስለሚያስከትል ሊቆም ይገባል ሲል  አሳስቧል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ በሚከበሩ ሕዝባዊና ሃይማኖታዊ በዓላት፣ ዓለም አቀፋዊና አህጉራዊ ጉባኤዎች እንዲሁም ከሌሎች ተመሳሳይ ኹነቶች ጋር በተያያዘ ውሎና አዳራቸውን በጎዳና ላይ ያደረጉ ሰዎችን በኃይል በማንሳት በአንድ ስፍራ እንዲቆዩ የማድረግ ስራ በተደጋጋሚ እንደሚከናወን መግለጫው አመላክቷል፡፡ ኢሰመኮ በታኅሣሥ ወር 2017 ዓ.ም ባደረጋቸው ክትትሎች በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ “ቃሊቲ አካባቢ” ተብሎ በሚጠራው የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ አካባቢ ሰፊ መጋዘን ውስጥ ከጎዳና ላይ የተነሱ በርካታ ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡ ወደ ማቆያው ከገቡት ሰዎች መካከል በማዕከሉ ከመቆየት እና የእርሻ ሥራ ከመሥራት እንዲመርጡ በማድረግ፤ የእርሻ…
Read More
የአማራ ዳኞች ማህበር የታሰሩ አባላቱ እንዲፈቱ ጠየቀ

የአማራ ዳኞች ማህበር የታሰሩ አባላቱ እንዲፈቱ ጠየቀ

የፌደራል መንግስት ክልል የክልል ልዩ ሀይሎችን ዳግም አደራጃለሁ በሚል ውሳኔ ካሳለፈበት ሚያዝያ 2015 ዓ.ም ጀምሮ በአማራ ክልል በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች አማካኝነት ጦርነት ተቀስቅሷል፡፡ በክልሉ ተጥሎ የነበረው የአስቸኳይ አዋጅ ከ10 ወራት በኋላ ያልተራዘመ ቢሆንም አሁንም በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ጦርነቶች እየተካሄዱ ናቸው፡፡ ከጦርነቱ ባለፈም በክልሉ ንጹሃን ዜጎች በጅምላ እየታሰሩ መሆኑን የገለጹ ሲሆን ከነዚህ ውስጥም የአማራ ዳኞች ማህበር እና ጤና ባለሙያዎች ማህበር አባላቶቻቸው ለተለያዩ ጉዳቶች መዳረጋቸውን ተናግረዋል፡፡ የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር እንዳለው በክልሉ ያለው የደህንነት ችግር ዳኞች በነጻነት ስራቸውን እንዳይሰሩ እክል መፍጠሩን ገልጾ ባለፉት ቀናት ውስጥም 13 ዳኞች ታስረዋል፡፡ ከታሰሩት ውስጥ አራት ዳኞች ከእስር መለቀቃቸውን የተናገረው ማህበሩ ቀሪ እና በእስር…
Read More
በኢትዮጵያ ኃይል የበዛበትና በንፁኃን ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እንዲቆም አሜሪካ አሳሰበች

በኢትዮጵያ ኃይል የበዛበትና በንፁኃን ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እንዲቆም አሜሪካ አሳሰበች

በኒውዮርክ እየተካሄደ ከሚገኘው 79ኛው የተመድ ጉባዔ ጎን ለጎን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የአፍሪካ ጉዳይ ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊ ከኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ጋር ተወያይተዋል፡፡ ሞሊ ፊ ከውይይቱ በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ በኢትዮጵያ ኃይል የበዛበት የመንግሥት ምላሽና ንፁኃን ላይ ያነጣጠረ የታጣቂዎች ጥቃት እንዲቆም አሳስበዋል። ረዳት ሚኒስትሯ ከሁለት ዓመታት በፊት የተካሄደውን የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በተሳካ ሁኔታ እንዲፈጸም፣ ከአፍሪካ ኅብረት ጋር በመሆን ያለ ማቋረጥ ውትወታ እናደርጋለንም ብለዋል። በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ያለውን ግጭት በተመለከተ ያለንን ሥጋት በመግለጽ እንዲቆም በግል በሚደረግ ውይይትና በይፋ በሚኖሩ መግለጫዎች እየጠየቁ መሆኑን አስታውቀዋል። ታጣቂዎች በንፁኃንና በመንግሥት መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እያደረሱ መሆኑን የገለጹት ሞሊ ፊ የመንግሥት…
Read More
በአማራ ክልል ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ ከ160 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ ከ160 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ካሳለፍነው ሰኔ ወር ጀምሮ በኢትዮጵያ የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ ኢሰመኮ በሪፖርቱ ላይ እንደጠቀሰው በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ደቡብ ምዕራብ፣ጋምቤላ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ላይ ከህግ ውጪ ግድያ፣ የዘፈቀደ እስር፣ እገታ፣ አስገድዶ መድፈር እና ሌሎች የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በንጹሀን ላይ ተፈጽመዋል ብሏል፡፡ ከሰኔ ወር ጀምሮ ባሉት ሶስት ወራት ውስጥ በአማራ ክልል በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል በተፈጠረው ጦርነት ከ160 በላይ ዜጎች መገደላቸውን ኢሰመኮ አስታውቋል፡፡ ግድያ ከተፈጸመባቸው ዜጎች መካከል የአዕምሮ ህመምተኞች፣ አዛውንቶች፣ ህጻናት እና ሴቶች እንደሚገኙበት ተገልጿል፡፡ ጎንደር፣ የጎጃም አካባቢዎች፣ ደብረሲና፣ አታዬ፣ ሸዋሮቢት እና ሌሎችም ቦታዎች ያሉ ሲሆን መረጃ ለፋኖ ትሰጣላችሁ፣ የመንግስት ጉዳይ አስፈጻሚ…
Read More
በአማራ ክልል ደብረሲና እና አዴት ከተሞች ከ27 በላይ ሰዎች በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች ተገደሉ

በአማራ ክልል ደብረሲና እና አዴት ከተሞች ከ27 በላይ ሰዎች በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች ተገደሉ

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ እና ሰሜን ጎጃም ዞኖች በቀናት ልዩነት “የመንግሥት ኃይሎች” ቤት ለቤትና መንገድ ላይ ‘ሰላማዊ ሰዎችን’ መግደላቸውን የዐይን እማኞችና ነዋሪዎች ተናግረዋል። ጥቃቶቹ ሰኞ ሰኔ 17 እና ረቡዕ ሰኔ 19፤ 2016 ዓ/ም መፈጸማቸው የተነገረ ሲሆን፤ በጥቃቶቹም ከ27 በላይ ንጹሃን ሰዎች እንደተገደሉ ተገልጿል። በሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ከደብረ ሲና ከተማ ወጣ ብላ በምትገኝ ሾላ ሜዳ በተባለች አነስተኛ የገጠር ከተማ ሰኔ 19 በመንግሥት ኃይሎች ደርሷል በተባለ ጥቃት ቢያንስ 15 ሰዎች መገደላቸውን እና አራት የሚሆኑ ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል። በከተማዋ ‘አጋም በር መገንጠያ’ በተባለ ሰፈር ጥቃቱ ምሽት 11፡30 አካባቢ እንደተፈጸመ የተናገሩ አንድ ከጥቃቱ የተረፉ እማኝ፤ በጥቃቱ በአብዛኛው ማዳበሪያ ለመውሰድ…
Read More
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ጉባኤ በመንግስት ጫና እየተደረገበት እንደሆነ ገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ጉባኤ በመንግስት ጫና እየተደረገበት እንደሆነ ገለጸ

የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ላይ የሚደረገው ወከባ እና እስር እንዲቆም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል ጠይቋል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) መንግስት ከፍተኛ ጥቃትና ጫና እየፈጸመበት እንደሆነ ባወጣው መግለጫ ገልጿል፡፡ ኢሰመጎ በመግለጫው በመንግስት እየደረሰበት ያለው ጥቃት እና ጫና አስጊ ደረጃ ላይ መድረሱን በመግለጫው ላይ አሳውቋል። ጉባኤው በተለያዩ ጊዜ ተፈጽመውብኛል ያላቸው ጥቃቶች እና ከፍተኛ ጫናዎች በመግለጫው ላይ የዘረዘረ ሲሆን በተቋሙ አመራር ላይ በመንግስት የደህንነት ሰዎች የሚፈጸም ክትትል ፣ ዛቻ እና ማስፈራሪያ እየጨመረ መምጣታቸውን አስታውቋል፡፡ እንዲሁም የሰብዓዊ መብት ክትትል ስራችሁን ካላቆማችሁ ፤ መንግሥትን በሰብዓዊ መብት ጥሰት መወንጀል ካላቆማችሁ  ' ዋጋ ትከፍላላችሁ ' የሚል ዛቻ እየደረሰበት መሆኑን ገልጿል፡፡ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የምርመራ ስራ በሚሰሩ…
Read More
በአማራ ክልል በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች የሚፈጸሙ ግድያዎች መቀጠላቸውን ኢሰመኮ ገለጸ

በአማራ ክልል በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች የሚፈጸሙ ግድያዎች መቀጠላቸውን ኢሰመኮ ገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ ክልል በቀጠለው ጦርነት ዙሪያ ያደረገውን የምርመራ ሪፖርት ይፋ አድርጓል፡፡ ኮሚሽኑ እንዳለው በአማራ ክልል ባለው ጦርነት የደረሱ ጉዳቶችን ለመመርመር መንግሥታዊ ኃላፊዎችን፣ በግጭቱ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎችን፣ የዐይን ምስክሮችን፣ ተጎጂዎችንና የተጎጂዎች ቤተሰቦችን በማነጋገር መረጃዎችንና ማስረጃዎችን ማሰባባቡን ገልጿል፡፡ ከሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ባለው ጊዜ ውስጥ በአማራ ክልል ሁሉም ዞኖች በመንግስት የጸጽታ ሀይሎች እና በተለምዶ ፋኖ በመባል ከሚታወቀው አካል ጋር ጦርነት እየተካሄደ መሆኑን ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡ ይህ ጦርነት በአንዳንድ አካባቢዎች በከባድ መሣሪያ እና አልፎ አልፎ በአየር/ድሮን ድብደባ ጭምር የታገዘ ነው ያለ ሲሆን በሲቪል ሰዎች ላይ ሞት እና የአካል ጉዳት መድረሱ ተገልጿል፡፡ በሰሜን ሸዋ ዞን፣ በረኸት ወረዳ፣ መጥተህ ብላ ከተማ፣…
Read More
በኢትዮጵያ የዘር ማጥፋት ወንጀል ከፍተኛ ስጋት መኖሩን ተመድ አስታወቀ

በኢትዮጵያ የዘር ማጥፋት ወንጀል ከፍተኛ ስጋት መኖሩን ተመድ አስታወቀ

በኢትዮጵያ በፌደራል መንግሥት የጸጥታ ሀይሎች እና በተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ ታጣቂዎች መካከል በቀጠለው ውጊያ ምክንያት፤ የዘር ማጥፋት እና ተያያዠ አሰቃቂ ወንጀሎች እንዲፈጸሙ የሚያስችል ከፍተኛ ስጋት መፍጠሩን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አማካሪ ገለጹ። የድርጅቱ የዘር ማጥፋት ወንጀል መከላከል ልዩ አማካሪ አሊስ ዋይሪሙ በኢትዮጵያ ስላለው ኹኔታ አስመልክተው ባወጡት መግለጫ፤ በትግራይ፣ አማራ፣ አፋር እና ኦሮሚያ ክልሎች እየተካሄዱ ባሉ ውጊያዎች ምክንያት በአገሪቱ ከፍተኛ የዘር ማጥፋት እና ተያያዠ አሰቃቂ ወንጀሎች የመፈጸም ኹኔታዎች እንዲኖሩ ማድረጉን ጠቁመዋል። "በኢትዮጵያ እየተፈጸሙ ስላሉት ወንጀሎች የተመለከቱ የሚደርሱን ሪፖርቶች እጅግ የሚረብሹ ናቸው" ያሉት ልዩ አማካሪዋ፤ "በአፋጣኝ ኹኔታውን ለመከላከል እርምጃ ሊወሰድ ይገባል።" ብለዋል። አክለውም፤ "እየደረሱን ካሉ ሪፖርቶች መካከል የአንድ ቤተሰብ አባላት በሙሉ ግድያ እንደተፈጸመባቸው፣ ቤተሰቦች…
Read More
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ እየተባባሰ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳሳሰበው ገለጸ

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ እየተባባሰ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳሳሰበው ገለጸ

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ እየተባባሳ ነው ያለው ወንጀልና የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳስጨነቀው ተናግሯል። የህብረቱ ከፍተኛ ተወካይ ጆሴፍ ቦሬል የኢትዮጵያ መንግስት አፋጣን እርምጃ መውሰድ አለበት ብለዋል። ፍትህና ተጠያቂነት የህብረቱና የኢትዮጵያ ግንኙነት ቀስ እያለ ወደ መደበኛነት ለሚመጣው ግንኙነት ሁኔታዎች ናቸውም ሲሉ ሀሳባቸውን በቀድሞው ትዊተር በአሁኑ ኤክስ ገልጸዋል። ከሰሞኑን በተመድ ጠቅላላ ጉባኤ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ሁኔታ የቀረበ ሲሆን፤ ሀገሪቱ ከፍተኛ ክስ ቀርቦባታል። በተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት የተቋቋመው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የኢትዮጵያ መሪማሪ ሪፖርቱን አቅርቧል። የመርማሪ ቡድኑ ባለሞያ የሆኑት መሀመድ ቻንዴ ኦቶማን ባለፈው ዓመት ለተመድ የሰብዓዊ ምክር ቤት የኢትዮጵያን ሁኔታ ከገለጽን ወዲህ ሰብዓዊ መብት በሀገሪቱ በእጅጉ ተባብሶ ቀጥሏል ብለዋል። በትግራይ ክልል…
Read More
ተመድ ኢትዮጵያ ወደ ሀገር አቀፍ ግጭት እያመራች ነዉ ሲል አስጠነቀቀ

ተመድ ኢትዮጵያ ወደ ሀገር አቀፍ ግጭት እያመራች ነዉ ሲል አስጠነቀቀ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ኢትዮጵያ ወደ ሀገር አቀፍ ግጭት እያመራች ነዉ ሲል አሳዉቋል። በአማራ እና ኦሮሚያ ክልል ያለዉም ግጭት ተበራክቷል ያለው ተመድ የግጭቶች መበራከት ኢትዮጵያን ወደ ሀገር አቀፍ መጠነ ሰፊ ግጭት ሊወስዳት ይችላል ሲልም አስጠንቅቋል። ከዚህ በተጨማሪም በአማራ ክልል ያለዉን ወቅታዊ ሁኔታ በማስመልከት ፤ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የጅምላ እስር እና እንግልት እየተፈጸመ እንደሆነም አስታውቋል። ድርጅቱ በመግለጫው አክሎም በክልሉ ፤ በመንግስት ቢያንስ አንድ ጊዜ የሰዉ አልባ አዉሮፕላን ጥቃት መፈጸሙን የደረሱኝ ሪፖርቶች ያመለክታሉ ሲልም ጠቅሷል። በአማራ ክልል በርከታ ከተሞችም ከሲቪል አስተዳደር ዉጪ በመሆን በወታደራዊ ስርዓት ስር ወድቀዋል ተብሏል። በአማራ ክልል የተፈጠረውን ጦርነት ተከይሎ ካሳለፍነው ሀምሌ ወር ጀምሮ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መደንገጉን ተከትሎ…
Read More