Tanzania

ኢትዮጵያ ከአንድ ወር በኋላ ለታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ሀይል መሸጥ እንደምትጀምር ገለጸች

ኢትዮጵያ ከአንድ ወር በኋላ ለታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ሀይል መሸጥ እንደምትጀምር ገለጸች

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሀይል የማመንጨት አቅም በዕጥፍ ጨምሯል ተብሏል ኢትዮጵያ ከታላቁ የህዳሴ ግድብ የምታመነጨውን የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን ከእጥፍ በላይ ማሳደጓን አስታወቀች። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ሥራ አስፈጻሚ አሸብር ባልቻ በሰጡት መግለጫ በቅርቡ ሁለት ተጨማሪ ተርባይኖች አገልግሎት በመጀመራቸዉ ከግድቡ የሚመረተዉ የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን ወደ 1 ሺሕ 550 ሜጋዋት ከፍ ብሏል። ከዚሕ ቀደም ሥራ የጀመሩት ሁለት ተርባይኖች እያንዳዳቸዉ 375 ሜጋዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ሲያመነጩ ቆይተዋል፡፡ ሰሞኑን የተመረቁት ሁለት ተጨማሪ ተርባይኖች ደግሞ እያንዳዳቸዉ 400 ሜጋዋት ኃይል እንደሚያመነጩ ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ ከግብፅና ሱዳን ጋር የሚያወዛግባትን ግዙፍ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ በአባይ ወንዝ ላይ መገንባት የጀመረችዉ ከመጋቢት 2003 ዓ.ም ጀምሮ ነበር። ይህ የአፍሪካ ትልቁ ግድብ በ2014 ዓ.ም ላይ…
Read More
ኢትዮጵያ ለታንዛንያ 400 ሜጋዋት ሀይል ለመሸጥ ተስማማች

ኢትዮጵያ ለታንዛንያ 400 ሜጋዋት ሀይል ለመሸጥ ተስማማች

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ባሳለፍነው ሳምንት በታንዛንያ ይፋዊ ጉብኝት አድርገው መመለሳቸው ይታወሳል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዳሬሰላም ቆይታቸው የአቪዬሽን እና ኤሌክትሪክ ሀይል ሽያጭ ስምምነት ከፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሐሰን መንግስት ጋር መፈጸማቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም ተናግረዋል፡፡ ቃል አቀባዩ በሰጡት ሳምንታዊ የዲፕሎማሲ መግለጫ ለይ እንዳሉት ኢትዮጵያ ለታንዛንያ 400 ሜጋዋት ሀይል ለመሸጥ ስምምነት ፈጽማለች ብለዋል፡፡ የኤሌክትሪክ ኃይል በተያዘው ዓመት ከሀገር ውስጥ እና ለውጭ ሀገራት ከተሸጠ የኤሌክትሪክ ሀይል ሽያጭ 30 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ማቀዱን አስታውቋል፡፡ ኢትዮጵያ በተያዘው በጀት ዓመት ሶስት ሺህ ጊጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ ጎረቤት ሀገራት በመላክ 182 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ማቀዷም ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ አሁን ላይ ለጅቡቲ፣…
Read More
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ታንዛኒያን እንደሚጎበኙ ተገለጸ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ታንዛኒያን እንደሚጎበኙ ተገለጸ

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ወደ ኬንያ ያመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በናይሮቢ ቆይታቸው ከፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በሁለትዮሽ እና አካባቢያዊ ጉዳዮች ዙሪያ እንደተወያዩ ሲገለጽ የተለያዩ ተቋማትንም ጎብኝተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ወደ ኬንያ ሲጓዙ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜያቸው ነው፡፡ የኢትዮጵያ እና ኬንያ ከ70 ዓመት በፊት ጀምሮ ጥብቅ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን ከአንድ ሳምንት በፊትም የኢትዮ ኬንያ ሚኒስትሮች ጉባኤ በአዲስ አበባ አካሂደዋል፡፡ ኢትዮጵያዊያን ያለ ቪዛ ወደ ኬንያ እንዲሁም ኬንያዊያን ወደ ኢትዮጵያ ያለቪዛ እንዲገቡ የሚፈቅድ የሁለትዮሽ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ…
Read More
የፌደራል መንግሥት እና ኦሮሚያ ነጻነት ሰራዊት ድርድር አለመሳካቱ ተገለጸ

የፌደራል መንግሥት እና ኦሮሚያ ነጻነት ሰራዊት ድርድር አለመሳካቱ ተገለጸ

የመንግስት ኮሙንኬሽን ጉዳዮች ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ በኦሮሚያ ክልል ያለውን ግጭት በማስወገድ ሰላምን ለማምጣት ያለመውና በታንዛኒያ ሲካሄድ የቆየው የሰላም ውይይት የመጀመሪያ ምዕራፍ ተጠናቋል ብሏል። ውይይቱ በአብዛኛው በአዎንታዊ መልኩ የተከናወነ ነው ያለው ሚንስቴሩ በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ግን በዚህኛው የውይይት ምዕራፍ ስምምነት ላይ አልተደረሰም ብሏል። ግጭቱን በዘላቂነትና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለማስቆም እንዲቻል ሁለቱም አካላት የሰላም ውይይቱን መቀጠል አስፈላጊ መሆኑ ላይ እንደተግባቡ ተገልጿል። በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥትና እስካሁን ሲመራባቸው በነበሩ መሠረታዊ መርሖች መሠረት ግጭቱን በሰላማዊ መልኩ ለመፍታት መንግስት የጸና አቋም እንዳለው በመግለጫው ላይ ተጠቅሷል። ይህንን መልካም አጋጣሚና በውይይት ችግሮችን የመፍታት በጎ ጅምር በመጠቀም ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ የኢትዮጵያ መንግሥት ፅኑ አቋም እንዳለው አስታውቋል። አሜሪካ በታንዛኒያ ራስ…
Read More
መንግስት ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋር እየተደረገ ስላለው ድርድር መረጃ እንዲሰጥ ተጠየቀ

መንግስት ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋር እየተደረገ ስላለው ድርድር መረጃ እንዲሰጥ ተጠየቀ

መንግሥት ‹‹ከኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት›› ጋር ስለሚያደርገው ድርድር በቂ መረጃ ይስጥ ሲል ኢዜማ አሳስቧል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) መንግሥት ራሱን ‹‹የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት›› ከሚለው ታጣቂ ቡድን ጋር ስለሚያደርገው ድርድር በቂ መረጃ ይስጥ ሲል ጠይቋል፡፡  ፓርቲው በተለይ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኦሮሚያ ክልል በተደጋጋሚ ዜጎች በማንነታቸው ምክንያት ሲገደሉ ንብረታቸውም ሲወድምና ከቀያቸው ሲፈናቀሉ በግልጽ ተመልክተናል ብሏል፡፡ መንግስትም በተደጋጋሚ የተፈፀሙትን በደሎች ይህ ታጣቂ ቡድን ሲፈፅማቸው እንደነበር ከማሳወቁ አንፃር ይህን መሰል የዜጎች ሰቆቃ የሚያስቆም ድርድር ውስጥ መግባቱን ፓርቲው እንደሚደግፈው ገልጿል፡፡  ይሁንና ብልጽግና ኢትዮጵያን መምራት ከጀመረበትን ጊዜ ጨምሮ ባለፉት አምስት ዓመታት በተለያየ ጊዜ የሚፈጸሙ ድርድሮች ግልጽነት የጎድላቸው እና አፈፃፀማቸው ደካማ መሆናቸውን ፓርቲው በመግለጫው አስታውቋል፡፡ ለአብነትም ከሕወሓት…
Read More