Militarydeal

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የጦር መሳሪያ ማዕቀብ አነሳች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የጦር መሳሪያ ማዕቀብ አነሳች

በኢትዮጵያ ላይ ተጥሎ የነበረው የጦር መሳሪያ ማዕቀብ መነሳቱን አሜሪካ አስታውቃለች። ማዕቀቡ መነሳቱን የገለፀው በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአገር መከላከያ ንግድ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ነው። ዳይሬክቶሬቱ፣ በኢትዮጵያ ላይ ይከተል የነበረውን የክልከላ ፖሊሲ በማንሳት አሁን ላይ በዓለም አቀፍ የጦር መሣሪያ ዝውውር ደንብ (ITAR) ቁጥጥር የሚደረግባቸውን እና ከኢትዮጵያ ጋር የተያያዙ የፈቃድ ማመልከቻዎችን በየተራ እየገመገመ ነው። ይህን ተከትሎ በቅርቡ በሚወጣ የደንብ ለውጥ፣ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የጦር መሳሪያ ዝውውር ደንብ - ITAR 126.1 ዝርዝር ውስጥ ከሚገኙ አገራት ተርታ "እንድትሰረዝ" የሚደረግ መሆኑን ጠቅሷል። ይህ ደንብ በአሜሪካ ማዕቀብ ስር የሚገኙ የተወሰኑ አገራት፤ ለመከላከያ ሠራዊት፣ ለፖሊስ፣ ለደህንነት እና ለሌሎችም የአገር ውስጥ የጸጥታ ኃይሎቻቸው የሚሆኑ የመከላከያ ቁሳቁሶችን እና አገልግሎቶችን ከውጭ…
Read More
ኢትዮጵያ እና ኬንያ ወታደራዊ ስምምነት ተፈራረሙ

ኢትዮጵያ እና ኬንያ ወታደራዊ ስምምነት ተፈራረሙ

ኢትዮጵያ እና ኬንያ ከ62 ዓመታት በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ታሪካዊ የሚባል ወታደራዊ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱ ከሁለቱ ሀገራት ባለፈ ለቀጠናው ሰላምና መረጋጋትም የጎላ ፋይዳ ያለው መሆኑም ተገልጿል። ስምምነቱን የኢትዮጵያ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና የኬንያ መከላከያ ኢታማዦር ሹም ጄነራል ቻርልስ ሙሪዩ ካሃሪሪ ፈርመዋል። ስምምነቱ ከሃገራቱ በተጨማሪ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የጎላ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ እና የኬንያ መከላከያ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ቻርልስ ሙሪዩ ካሃሪሪ ተናግረዋል። በቀጣይም ከኢትዮጵያ መከላከያ ጋር በትብብር በሚሰሩ ስራዎች ዙሪያ የኬንያ መከላከያ በቁርጠኝነት ለመስራት ፍላጎት ያለው መሆኑን ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ቻርልስ ሙሪዩ ካሃሪሪ መናገራቸውንም ከኢኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የተገኘው መረጃ ያመላክታል። ኢትዮጵያና…
Read More