24
Nov
ከአንድ ሳምንት በፊት የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ዮሪ ሙሴቪኒ ሀገራቸው የባህር በር ካላገኘች ከኬንያ ጋር ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል ሲሉ ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል። ኬንያ ለኡጋንዳ ጥያቄ በይፋ መልካም ምላሽ ሰጥታለች። የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ጎረቤቷ ለሆነችው ኡጋንዳ የባሕር በር እንደምትሠጥ አስታውቀዋል። ኡጋንዳ በኬንያ በኩል በነዳጅ ቧንቧ፣ በመንገድ እና በባቡር ሐዲድ አማካኝነት በሕንድ ውቅያኖስ ላይ የባሕር በር እንድታገኝ እናደርጋለን ብለዋል ፕሬዝዳንት ሩቶ። ኬንያ ለኡጋንዳ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ሲባል የነዳጅ ማስተላለፊያ ቧንቧዋን የሚያስተዳድረውን መንግሥታዊ ኩባንያ ከኡጋንዳ ጋር በጋራ ባለቤትነት ለመያዝ ፍቃደኛ መኾኗንም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል። ኬንያ በቻይና እርዳታ የተዘረጋውን የባቡር ሐዲዷን በቅርቡ እስከ ኡጋንዳ መዲና ካምፓላ ከተማ ድረስ እንደምትዘጋም በፕሬዝዳንቷ በኩል አስታውቃለች። ሌላኛዋ ወደብ አልባ ሀገር ኢትዮጵያ…