Uganda

ኬንያ ለኡጋንዳ የባህር በር እንደምትሰጥ አስታወቀች

ኬንያ ለኡጋንዳ የባህር በር እንደምትሰጥ አስታወቀች

ከአንድ ሳምንት በፊት የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ዮሪ ሙሴቪኒ ሀገራቸው የባህር በር ካላገኘች ከኬንያ ጋር ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል ሲሉ ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል። ኬንያ ለኡጋንዳ ጥያቄ በይፋ መልካም ምላሽ ሰጥታለች። የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ጎረቤቷ ለሆነችው ኡጋንዳ የባሕር በር እንደምትሠጥ አስታውቀዋል። ኡጋንዳ በኬንያ በኩል በነዳጅ ቧንቧ፣ በመንገድ እና በባቡር ሐዲድ አማካኝነት በሕንድ ውቅያኖስ ላይ የባሕር በር እንድታገኝ እናደርጋለን ብለዋል ፕሬዝዳንት ሩቶ። ኬንያ ለኡጋንዳ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ሲባል የነዳጅ ማስተላለፊያ ቧንቧዋን የሚያስተዳድረውን መንግሥታዊ ኩባንያ ከኡጋንዳ ጋር በጋራ ባለቤትነት ለመያዝ ፍቃደኛ መኾኗንም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል። ኬንያ በቻይና እርዳታ የተዘረጋውን የባቡር ሐዲዷን በቅርቡ እስከ ኡጋንዳ መዲና ካምፓላ ከተማ ድረስ እንደምትዘጋም በፕሬዝዳንቷ በኩል አስታውቃለች። ሌላኛዋ ወደብ አልባ ሀገር ኢትዮጵያ…
Read More
የዓለም ገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ ጉባኤ በኡጋንዳ እየተካሄደ ነው

የዓለም ገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ ጉባኤ በኡጋንዳ እየተካሄደ ነው

የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ ወይም በምህጻረ ቃሉ ናም በመባል የሚታወቀው ይህ ተቋም በፈረንጆቹ 1961 ላይ የተቋቋመ ሲሆን ዓለምን ከቀዝቃው ጦርነት ድባቴ ማውጣት ደግሞ ለድርጅቱ መመስረት ዋነኛ ምክንያት ነበር፡፡ 120 ሀገራትን በአባልነት የያዘው ይህ ንቅናቄ በታዳጊ ሀገራት ላይ የሚደርሱ ጭቆናዎችን በጋራ መታገል፣ ጸረ ቅኝ ግዛት ትግሎችን መደገፍ እና የነጻ ሀገር ምስረታን ማበረታታትም ሌላኛው ዓላማውም ነው፡፡ ከመንግስታቱ ድርጅት በመቀጠል በርካታ ሀገራትን በአባልነት የያዘው ይህ ንቅናቄ ዋና መቀመጫውን ምስራቅ አውሮፓዊቷ የቀድሞዋ ዩጎዝላቪያ አሁን ደግሞ የሰርቢያ ዋና ከተማ ቤልግሬድ አድርጎ ተመስርቷል፡፡ ድርጅቱ እንዲመሰረትም የቀድሞው የዩጎዝላቪያ ፕሬዝዳንት  ጆሴፍ ቲቶ፣ የሕንዱ ጃዋህራል ኔህሩ፣ የግብጹ ገማል ናስር፣ የጋናው ክዋሜ ንኩሩማህ እና የኢንዶኔዢያው ሱካርኖ ዋና መስራች መሪዎች እና ሀገራት…
Read More
ኡጋንዳውያን የዓለም ፍጻሜ ደርሷል በሚል ወደ ኢትዮጵያ መፍለሳቸው ተገለጸ

ኡጋንዳውያን የዓለም ፍጻሜ ደርሷል በሚል ወደ ኢትዮጵያ መፍለሳቸው ተገለጸ

በመቶዎች የሚቆጠሩ የኡጋንዳ የሐይማኖት ኑፋቄ አባላት የምፅዓት ቀንን በመስጋት ወደ ኢትዮጵያ እየተሰደዱ ነው ተብሏል፡፡ የኑፋቄ መሪዎቹ የዓለም መጨረሻ እንደቀረበና ሞትም አካባቢያቸውን እንደሚመታ አሳምኗቸዋል። በኡጋንዳ ምስራቃዊ ክፍል ውስጥ የሚገኙ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከቀያቸው ወደ ኢትዮጵያ መሰደዳቸውን የኡጋንዳ ፖሊስ አስታወቋል። ፖሊስ ባደረገው ምርመራ የኑፋቄው አባላት ከአካባቢያቸው ይጀመራል ብለው ካመኑበት የዓለም ፍጻሜ ለማምለጥ ሸሽተዋል ብሏል። የኑፋቄው አባላት በቅርቡ አካባቢያቸው በሞት እንደሚመታ እና ሁሉም ሰዎች እንደሚሞቱ በመሪዎቹ እንደተነገራቸው ገልፀዋል። ንብረታቸውን ሸጠው ወደ ኢትዮጵያ መሰደዳቸው የተነገረው አነዚህ ኡጋንዳውያን ከዚያም ካሉበት በኡጋንዳ ከሚገኙ አንዳንድ ዘመዶቻቸው ጋር እየተነጋገሩ ነው። “የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት ቤተክርስቲያን በሚባል የሃይማኖት ኑፋቄ ላይ በኡጋንዳ ምስራቃዊ ሴሬሬ ወረዳ በኦቡሉም መንደር ውስጥ የሚገኘውን የሃይማኖት ክፍል…
Read More