Religion

የትግራይ አህጉረ ስብከት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓትን እንዲያከብር ቋሚ ሲኖዶስ ጠየቀ

የትግራይ አህጉረ ስብከት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓትን እንዲያከብር ቋሚ ሲኖዶስ ጠየቀ

የትግራይ አህጉረ ስብከት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓትን እንዲያከብር ቋሚ ሲኖዶስ ጠየቀ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ከሰሞኑ በትግራይ አህጉረ ስብከት በተሰጠ መግለጫ ዙሪያ ምላሽ ሰጥታለች። ቤተ ክርስቲያኗ በመግለጫዋ እንዳለችው በጦርነቱ ምክንያት በቤተ ክርስቲያኒቱ የበላይ መዋቅርና በትግራይ ክልል አህጉረ ስብከት መካከል አስተዳደራዊና መዋቅራዊ ግንኙነት ተቋርጦ መቆየቱን ገልጻለች። ይህንንም ተከትሎ በጦርነቱ ምክንያት ሁሉም የባንክ ተቋማት ሥራቸውን በማቆማቸው በየጊዜው እንደሌሎች አህጉረ ስብከት ለትግራይ አህጉረ ስብከት ይላክ የነበረው በጀት መላክ አልተቻለም ተብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቀጣይ እርምጃ ምንድን ነው? ቤተክርስቲያኗ ተፈጥሮ የነበረውን ችግር በቀኖናው መሰረት መፈታቱን ገለጸችምንም እንኳን በባንክ መዘጋት ለአገልጋይ ሠራተኞች በጀት መላክ ባይቻልም የደመወዝ መክፈያ የባንክ…
Read More
ኡጋንዳውያን የዓለም ፍጻሜ ደርሷል በሚል ወደ ኢትዮጵያ መፍለሳቸው ተገለጸ

ኡጋንዳውያን የዓለም ፍጻሜ ደርሷል በሚል ወደ ኢትዮጵያ መፍለሳቸው ተገለጸ

በመቶዎች የሚቆጠሩ የኡጋንዳ የሐይማኖት ኑፋቄ አባላት የምፅዓት ቀንን በመስጋት ወደ ኢትዮጵያ እየተሰደዱ ነው ተብሏል፡፡ የኑፋቄ መሪዎቹ የዓለም መጨረሻ እንደቀረበና ሞትም አካባቢያቸውን እንደሚመታ አሳምኗቸዋል። በኡጋንዳ ምስራቃዊ ክፍል ውስጥ የሚገኙ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከቀያቸው ወደ ኢትዮጵያ መሰደዳቸውን የኡጋንዳ ፖሊስ አስታወቋል። ፖሊስ ባደረገው ምርመራ የኑፋቄው አባላት ከአካባቢያቸው ይጀመራል ብለው ካመኑበት የዓለም ፍጻሜ ለማምለጥ ሸሽተዋል ብሏል። የኑፋቄው አባላት በቅርቡ አካባቢያቸው በሞት እንደሚመታ እና ሁሉም ሰዎች እንደሚሞቱ በመሪዎቹ እንደተነገራቸው ገልፀዋል። ንብረታቸውን ሸጠው ወደ ኢትዮጵያ መሰደዳቸው የተነገረው አነዚህ ኡጋንዳውያን ከዚያም ካሉበት በኡጋንዳ ከሚገኙ አንዳንድ ዘመዶቻቸው ጋር እየተነጋገሩ ነው። “የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት ቤተክርስቲያን በሚባል የሃይማኖት ኑፋቄ ላይ በኡጋንዳ ምስራቃዊ ሴሬሬ ወረዳ በኦቡሉም መንደር ውስጥ የሚገኘውን የሃይማኖት ክፍል…
Read More