25
Apr
ኢትዮ ቴሌኮም ከ47 ሺህ በላይ የሚሆኑ ዜጎች ባለድርሻ መሆናቸውን ገልጿል። የኢትዮ ቴሌኮም 10 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ ሽያጭ ጥቅምት 6 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ በማስጀመር የአክሲዮን ሽያጩን እስከ ታኅሣስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ማከናወኑ ይታወሳል፡፡ በመቀጠልም ውጤቱን ለሚመለከተው የመንግስት አካል እና ለኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣንበማቅረብ እና በመገምገም በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት የሽያጭ ቀነ-ገደቡን በማራዘም እስከ የካቲት7 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ማለትም ለ121 ቀናት በዲጂታል መንገድ ሲከናወን መቆየቱ ይታወሳል፡፡ በዚህም መሰረት የተከናወነው የኢትዮ ቴሌኮም የአክሲዮን ሽያጭ ውጤት በየደረጃው በሚገኙየመንግስት አካላት ተገምግሞ እንዲሁም በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ታይቶ ውጤቱ ለህዝብ ይፋ እንዲደረግ አቅጣጫ መቀመጡ ተገልጿል፡፡ ከ47 ሺህ በላይ ዜጎችን በኢትዮ ቴሌኮም ውስጥ የባለቤትነት…