Telecomservice

ኢትዮ ቴሌኮም ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 62 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን ገለጸ።

ኢትዮ ቴሌኮም ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 62 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን ገለጸ።

በስመኝሽ ገብረወልድ ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲመሳከር የ 43.3 በመቶ ወይም 18.9 ቢሊዮን ብር እድገት አሳይቷል ብሏል። ገቢውም የእቅዱን 90.7 መሆኑን ተናግሯል። በዘንድሮ የበጀት ዓመት ስድስት ወር ውስጥ ምንም አይነት የሳይበር ጥቃት አልደረሰብኝም ነው ያለው። በዚሁ የስራ አፈፃፀም የግዜ ማዕቀፍ 6 ሚሊዮን ገደማ ደንበኞች አፍርቻለሁ ያለው ኩባንያው በአጠቃላይ የደንበኞቼ ቁጥርም 80.5 ሚሊየን ደርሰዋል ተብሏል። ኢትዮ ቴሌኮም በቴሌኮም አገልግሎት ብዛት ከአፍሪካ 1ኛ ከዓለም ደግሞ 17ኛ ደረጃ ላይ መቀመጡን ዓለም አቀፉ የቴሌኮም አገልግሎት ድርጅት ወይም ጂ.ኤስ.ኤም.ኤ (GSMA) ጥናት ተረጋግጧል ተብሏል። የደንበኛን ቁጥር ለመጨመር ከተሰሩት ስራዎች መካከል በግማሽ አመቱ 202 አዳዲስ የሞባይል ጣቢያዎች ተጠናቀው ወደ እንደገቡም ተገልጿል። በሞባይል ኔትዎርክ በተከናወኑ የፕሮጀክት…
Read More
የፈረንሳዩ ኩባንያ የኢትዮ ቴሌኮምን ድርሻ ለመግዛት የጀመረውን ጥረት እቅድ ሰረዘ

የፈረንሳዩ ኩባንያ የኢትዮ ቴሌኮምን ድርሻ ለመግዛት የጀመረውን ጥረት እቅድ ሰረዘ

ኦሬንጅ የተሰኘው የፈረንሳይ የቴሌኮም ኩባንያ ከኢትዮቴሌኮም 45 በመቶ አካባቢ ድርሻ ለመግዛት ዕቅድ የነበረው ቢሆንም ኃሳባችንን በፍጥነት ለመተግበር እና ውጤት ለማግኘት የሚያስችል ሁኔታ ባለመኖሩ ራሴን አግልያለሁ ብሏል። ኢትዮጵያ ከመንግስታዊው ኢትዮቴሌኮም እና በቅርቡ ገበያውን ከተቀላቀለው ከሳፋሪኮም በተጨማሪ ሦስተኛ የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ ስራ እንዲጀምር ፈቃድ ለመስጠት ገበያውን እየገመገመ የቆየች ሲሆን በቅርቡ የገበያው ሁኔታ የታሰበውን ያህል አመርቂ ባለመሆኑ ሐደቱ ተቋርጧል ማለቷ ይታወሳል። ከዚህ ጎን ለጎን ከኢትዮቴሌኮም ከግማሽ ያነሰ ድርሻ ለመሸጥም እየጣረች ሲሆን ኦሬንጅ ድርሻ ለመግዛት ፍላጎት ካሳዩት ዓለምአቀፍ ግዙፍ ኩባንያዎች መካከል አንዱ ነበር። ኩባንያው ሞባይል ለዎርልድ ላይቭ እንደገለፀው ከ2021 ጀምሮ የነበረውን ፍላጎት አሁን መግታቱን ይፋ አድርጓል። ኦሬንጅ ግሩፕ በጉዳዩ ላይ ትንተና ከሠራ በኋላ “ስትራቴጂያችንን…
Read More
ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን ሾመ

ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን ሾመ

ከሁለት ዓመት በፊት ወደ ኢትዮጵያ የገባው ሳፋሪኮም ቴሌኮም ኩባንያ አዲስ ሀላፊ ሾሟል። ላለፉት ሶስት ዓመታት በፈረንሳይ የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩት አምባሳደር ሔኖክ ተፈራ በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አዲስ ሀላፊነት ተሰጥቷቸዋል። አምባሳደር ሔኖክ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የውጭ ጉዳዮች እና ቁጥጥር ሀላፊ ሆነው ተሹመዋል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ለኢትዮ ነጋሪ እንዳረጋገጠው አምባሳደር ሔኖክ የቀድሞውን የድርጅቱ መሪ የነበሩት ማቲው ሀሪሰንን ተክተዋል። አምባሳደር ሔኖክ ተፈራ ከ2018 እስከ 2022 ድረስ በፈረንሳይ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው አገልግለዋል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከ20 በላይ ከተሞች የቴሌኮም አገልግሎት በመስጠት ላይ ሲሆን በቅርቡም በኤምፔሳ አማካኝነት የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ፈቃድ ከብሔራዊ ባንክ እንደሚያገኝ ተገልጿል።
Read More