Nationalbankofethiopia

ብሔራዊ ባንክ የኢንሹራንስ ባለአክሲዮኖችን ለመመዘን አዲስ መመሪያ አወጣ

ብሔራዊ ባንክ የኢንሹራንስ ባለአክሲዮኖችን ለመመዘን አዲስ መመሪያ አወጣ

ብሔራዊ ባንክ ያወጣው አዲስ መመሪያ በኢንሹራንስ ዘርፉ ላይ ግልጽነትን፣ ተጠያቂነትን እና የተጠናከረ የኮርፖሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያለመ ነው ብሏል። በዚህ መመሪያ መሠረትም ማንኛውም የኢንሹራንስ ኩባንያ የቦርድ አባላት ስብጥር አንድን ጾታ ብቻ የያዘ መሆን የለበትም። እያንዳንዱ የኢንሹራንስ ኩባንያ ቢያንስ ሁለት ሴት የቦርድ አባላት ሊኖሩት እንደሚገባ መመሪያው የግዴታ መስፈርትን አስቀምጧል። በተጨማሪም አንድ የቦርድ አባል ለመሆን ዝቅተኛው የዕድሜ ገደብ 30 ዓመት መሆን እንዳለበት ተደንግጓል። እያንዳንዱ የኢንሹራንስ ኩባንያ ሦስት ገለልተኛ የቦርድ አባላት ሊኖሩት ይገባል የተባለ ሲሆን እነዚህ ግለሰቦች የሁለተኛ ዲግሪ ያላቸው እና በፋይናንስ ዘርፍ ወይም ተያያዥ መስኮች የ10 ዓመት የሥራ ልምድ ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል ተብሏል። እንደ መመሪያው ከሆነ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ የውጭ ሀገር ዜጎች በገለልተኛ የቦርድ…
Read More
አንድ የአሜሪካ ዶላር ዋጋ ወደ 156 ብር ከፍ ማለቱ ተገለጸ

አንድ የአሜሪካ ዶላር ዋጋ ወደ 156 ብር ከፍ ማለቱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባከናወነው 20ኛው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ፣ አንድ የአሜሪካ ዶላርን አማካይ በ155 ነጥብ 4 ብር መድረሱን ይፋ አድርጓል። ብሔራዊ ባንክ ለገበያ ያቀረበው የውጭ ምንዛሬ መጠን 70 ሚሊዮን ዶላር ቢሆንም፣ ከንግድ ባንኮች በኩል የቀረበው የፍላጎት መጠን ግን 177 ነጥብ 12 ሚሊዮን ዶላር ሆኖ ሆኗል። ይህም አቅርቦቱ ከፍላጎቱ ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ልዩነት እንዳለው ያሳያል። ከፍተኛው የማሸነፊያ ዋጋ 156 ነጥብ 05 ብር ሲሆን ዝቅተኛው የጨረታ ዋጋ ደግሞ 153 ነጥብ 8805 ብር ሆኗል። ባንኩ በዚህ ጨረታ አንድ ዶላርን 155 ነጥብ 88 ብር መሸጡን አስታውቋል። በዚሁ ጨረታ ላይ በአጠቃላይ 20 የንግድ ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን፣ ካቀረቡት የዋጋ ተወዳዳሪነት አንጻር 9 ባንኮች ብቻ የቀረበውን የውጭ…
Read More
ብሔራዊ ባንክ የባንክ አካውንት ከብሔራዊ መታወቂያ ጋር እንዲያስተሳስሩ አሳሰበ

ብሔራዊ ባንክ የባንክ አካውንት ከብሔራዊ መታወቂያ ጋር እንዲያስተሳስሩ አሳሰበ

ባንኮች የከፈቷቸውን አካውንቶች በሁለት ሳምንት ውስጥ ከብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ጋር የማስተሳሰር ሥራ እንዲያጠናቅቁ ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል። ብሔራዊ ባንክ እና የብሔራዊ መታወቂያ በጋራ ባወጡት አዲስ የአተገባበር ሥርዓት መሰረት የፋይናንስ ተቋማት ብሄራዊ ኦፕሬተር በሆነው ኢት-ስዊች በኩል ከብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ጋር የማስተሳሰር ሥራ መስራት መጀመራቸው ተገልጿል። እስካሁን 10 የሚሆኑ የፋይናንስ ተቋማት ከብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ጋር የማስተሳሰሩን ሥራ ጨርሰዋል ሲባል ሌሎች ባንኮች በሙከራ ደረጃ ላይ ይገኛሉ። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ይለበስ አዲስ ለኢትዮ ነጋሪ እንደገለጹት ይህ አሰራር ባንኮች አገልግሎታቸው ቀልጣፋ እንዲሆንና ማዕከላዊ የመረጃ አያያዝ እንዲኖር ያስችላል ሲሉ ገልጸዋል። አክለውም ትስስሩ ባንኮች ከደንበኞቻቸው ጋር ያላቸውን አገልግሎት ያሳልጥላቸዋል፤ ወጪንም ይቆጥብላቸዋል ብለዋል፡፡ የኢት-ስዊች ቺፍ ፖርት ፎልዮ ኦፊሰር…
Read More
የባንኮች ብድር ዕድገት ጣሪያ ወደ 24 በመቶ አደገ

የባንኮች ብድር ዕድገት ጣሪያ ወደ 24 በመቶ አደገ

ብሔራዊ ባንክ አሁን ያለውን የዋጋ ግሽበት የመርገብ አዝማሚያ ለማስቀጠል እና የፋይናንስ ዘርፉን ጤናማነት ለመጠበቅ በመስከረም ወር ላይ ሊነሣ ይችላል ተብሎ የተገመተዉ የባንኮች ዓመታዊ የብድር ዕድገት ጣሪያን ሙሉ ለሙሉ ከማንሳት ይልቅ ገደቡ ለጊዜው ከ18 በመቶ ወደ 24 በመቶ ከፍ እንዲል ወስኗል፡፡ የባንኮች የብድር ዕድገት ገደብ መነሣት የብሔራዊ ባንክን የገንዘብ ፖሊሲ አቋም ለማመልከትና የገንዘብ ፖሊሲ መዋቅሩን የተሻለ ለማድረግ እንደሚረዳ ይታመናል ሲል ኮሚቴው አስረድቷል፡፡ ኮሚቴው  በጉዳዩ ላይ በወደፊት ስብሰባዎቹ ገምግሞ የውሳኔ ሐሳብ አንደሚያቀርብም ጠቅሷል፡፡ የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ተመን አሁን ባለበት 15 በመቶ እንዲቆይም ወስኗል፡፡ ብሔራዊ ባንክ ለሚሰጣቸው የተቀማጭ ሂሳብ አገልግሎት እና የብድር አገልግሎት የሚከፈሉ የወለድ ተመኖች ባሉበት እንዲቀጥሉ፤ እንዲሁም ባንኮች በብሔራዊ ባንክ የሚያስቀምጡት…
Read More
ብሔራዊ ባንክ በባንኮች ላይ የጣለውን አስገዳጅ የቦንድ ግዥ አነሳ

ብሔራዊ ባንክ በባንኮች ላይ የጣለውን አስገዳጅ የቦንድ ግዥ አነሳ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ በሁሉም ንግድ ባንኮች ላይ የተጣለው አስገዳጅ የቦንድ ግዥ እንዲነሳ መወሰኑን ገልጿል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ባደረገው ውይይት የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል። ከእነዚህም ውስጥ አንዱ ሁሉም ንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ (Treasury Bond) እንዲገዙ የሚያስገድደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ (MFAD/TRBO/001/2022) እንዲነሳ ያሳለፈው ወሳኔ ተጠቃሽ ነው። "አሁን ላይ የመንግሥት ገቢ የማሰባሰብ አቅም በእጅጉ በመሻሻሉ፣ እንዲሁም መንግሥት የበጀት ጉድለቱን ለሟሟላት የውጭና ገበያ መር የሆኑ የሀገር ውስጥ የመበደሪያ አማራጮችን እየተጠቀመ በመሆኑ በባንኮች ላይ ተጥሎ የቆየውን ይህ አስገዳጅ መመሪያ አሁን ላይ ማንሣቱ ተገቢ መሆኑን ኮሚቴው አምኖበታል" ሲል መግለጫው ጠቅሷል። ኮሚቴው ያመነበት ይህ የገንዘብ…
Read More
ኢትዮጵያ በውጭ ባንኮች ላይ የአምስት ቢሊዮን ብር ግዴታ ጣለች

ኢትዮጵያ በውጭ ባንኮች ላይ የአምስት ቢሊዮን ብር ግዴታ ጣለች

ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ የውጪ ባንኮች አምስት ቢሊዮን ብር ዝቅተኛ ካፒታል ሟሟላት እንደሚኖርባቸው ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ያወጣው አዲስ መመሪያ ጥብቅ ቅደመ ሁኔታዎችን ያስቀመጠ ነው ተብሏል። መመሪያው በባንኩ ዘርፍ የውጭ ሀገራት ተሳትፎን የውጭ ባንክ ተቀጥላ፣ የውጭ ባንክ ቅርንጫፍ እና የእንደራሴ ቢሮ ብሎ የሚከፍል ሲሆን ወደ ሥራ ከመግባታቸው በፊት የወንጀል እና የታክስ ማጣራትን ጨምሮ ጥብቅ ምርምራዎችን ማለፍ እንደሚጠበቅባቸው አስቀምጧል። የውጭ ባንኮች የደንበኞቻቸውን መረጃ በኢትዮጵያ ድንበር ውስጥ ብቻ ለማስቀመጥ እና ለመጠቀም ይገደዳሉ የተባለ ሲሆን ክፍያን በተመለከተ ከውጭ የሚገቡ ባንኮች ለምርመራ 200 ሺህ፣ ለፈቃድ 400 ሺህ እና ለእድሳት 400 ሺህ ብር መክፈል እንዳለባቸው ተቀምጧል። መመሪያው የሀገር ውስጥ ባንኮች ካፒታላቸውን መጨመር፣ የመረጃ አጠቃቀም ሕጋቸውን ከሀገሪቱ…
Read More
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የ50 ሚሊዮን ዶላር ጨረታ እንደሚያወጣ ገለጸ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የ50 ሚሊዮን ዶላር ጨረታ እንደሚያወጣ ገለጸ

ብሔራዊ ባንክ የዶላር ጨረታ በየ15 ቀኑ በተከታታይ አወጣለሁም ብሏል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በየሁለት ሳምንት መደበኛ የውጭ ምንዛሪ ሽያጭ ጨረታ ማካሄድ እንደሚጀምር አስታወቀ። ጨረታዎቹ ለሚቀጥሉት በርካታ ወራት የሚካሄዱ ሲሆን፣ ዓላማውም የማዕከላዊ ባንኩን የተረጋጋ የውጭ ምንዛሬ ስርዓት ግብን ለማሳካት ነው ብሏል። የማዕከላዊ ባንኩ የውጭ ምንዛሪ መጠባበቂያ ክምችት በታሪኩ ከፍተኛው እንደሆነ ገልጾ በተለይ ከቅርብ ወራት ወዲህ፣ በሀገሪቱ ውስጥ ብቸኛው የወርቅ ገዥ ለሆነው ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የቀረበው የወርቅ መጠን ከፍተኛ መሆን የሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ መጠባበቂያ ክምችት ከተገመተው በላይ እንዲጨምር እንዳደረገው ጠቁሟል። ከዚህ ከተጠበቀው በላይ ከሆነው የውጭ ምንዛሪ ግኝት አንጻር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በቀጣይ ወራት በመደበኛነት በየሁለት ሳምንቱ የውጭ ምንዛሪ ሽያጭ ጨረታዎችን ለማካሄድ መወሰኑን አሳውቋል።…
Read More
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 60 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ አቀረበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 60 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ አቀረበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ነገ እንደሚያካሂድ ገልጿል፡፡ 60 ሚሊየን ዶላር በነገው ዕለት በሁሉም ባንኮች ለጨረታ እንደሚቀርብ ባንኩ አስታውቋል። ባንኩ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ፕሮግራምን ተከትሎ የኢትዮጵያ የውጭ ክፍያ ሚዛን በተለይም የወጪ ንግድ፣ ሐዋላና የካፒታል ፍሰት በከፍተኛ ደረጃ መሻሻል ማሳየቱን ጠቅሷል። በተለይም ከቅርብ ወራት ወዲህ ወርቅን ወደ ውጭ የመላክ ብቸኛ ሥልጣን ላለው ብሔራዊ ባንክ የሚቀርበው የወርቅ መጠን በመጨመሩ ምክንያት የባንኩ ዓለም አቀፍ የውጭ ምንዛሪ መጠባበቂያ ክምችት መጨመሩን ገልጿል። በመሆኑም ከባንኩ የወርቅ ግዥ ጋር በተያያዘ የሚከሰተውን የገንዘብ አቅርቦት ዕድገት ለማገናዘብና በማዕከላዊ ባንኩ እጅ ካለው ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ክምችት ከፊሉን ለግሉ ዘርፍ በመስጠት በገበያው ላይ የውጭ ምንዛሪ አቅርቦትን ለማሻሻል ባንኩ የተወሰነ…
Read More
28 የኢትዮጵያ ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ተጭበርበሩ

28 የኢትዮጵያ ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ተጭበርበሩ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዓመታዊ የገንዘብ ደህንነት ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ የባንኩ ሪፖርት እስከ ሰኔ 2024 ድረስ ያሉ የገንዘብ እንቅስቀሴዎች ዙሪያ ትኩረቱን አድርጓል፡፡ ባንኩ በሪፖርቱ ላይ እንደጠቀሰው 28 የኢትዮጵያ ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በአጭበርባሪዎች ገንዘባቸውን አጥተዋል ብሏል፡፡ የማጭበርበር ድርጊቶቹ የተፈጸሙት በሐሰተኛ የገንዘብ ኖቶች፣ በተሰረቁ የኤትኤም ማሽኖች፣ በሐሰተኛ ቼኮች፣ በሐሰተኛ የስልክ መልዕክት እና ተያያዥ መንገዶች አማካኝነት ነው፡፡ በዚህ ዓመት ባንኮች ያጡት ገንዘብ ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ300 ሚሊዮን ብር ጭማሪ እንዳሳየም በሪፖርቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡ በኢትዮጵያ በአጠቃላይ ካሉ 31 ባንኮች ውስጥ 28ቱ ሲጭበረበሩ የቀሪዎቹ ሶስት ባንኮች ማንነት ግን በሪፖርቱ ላይ አልተጠቀሰም፡፡ ባንኮች ከአነስተኛ የብድር እና ቁጠባ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ብድሮችን እየሰጡ…
Read More
የአፍሪካ እና መካከለኛው ምስራቅ ባንኮች ወደ የኢትዮጵያ ለመግባት እያሰቡ ነው ተባለ

የአፍሪካ እና መካከለኛው ምስራቅ ባንኮች ወደ የኢትዮጵያ ለመግባት እያሰቡ ነው ተባለ

ኢትዮጵያ እስካሁን በሯን ለውጭ ባንኮች ዝግ አድርጋ የቆየች ሲሆን አሁን ላይ የፖሊሲ ማሻሻያ ከተደረገ በኋላ የውጭ ሀገራት ባንኮች እንዲገቡ ምቹ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ መሆኑን ብሔራዊ ባንክ ከዚህ በፊት መግለጹ ይታወሳል፡፡ ለዚህም ሲባል የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ከአንድ ዓመት በፊት የተቋቋመ ሲሆን ዋና መቀመጫውን በደቡብ አፍሪካ ያደረገው ስታንዳርድ ባንክ በኢትዮጵያ ለመግባት ከስድስት ወራት በፊት አመልክቷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ የሞሮኮ፣ የኬንያ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ባንኮች በኢትዮጵያ የመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው መግለጻቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዋና ገዢ ማሞ ምህረቱ ተናግረዋ፡፡ ዋና ገዢው አክለውም የውጭ ሀገራት ባንኮች በኢትዮጵያ እንዲሰሩ የሚፈቅደው ህግ በቀጣዮቹ ሳምንታት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚጸድቅ ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ባንክ ፍቃድ ለማግኘት የሚፈልጉ…
Read More