Nationalbankofethiopia

28 የኢትዮጵያ ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ተጭበርበሩ

28 የኢትዮጵያ ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ተጭበርበሩ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዓመታዊ የገንዘብ ደህንነት ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ የባንኩ ሪፖርት እስከ ሰኔ 2024 ድረስ ያሉ የገንዘብ እንቅስቀሴዎች ዙሪያ ትኩረቱን አድርጓል፡፡ ባንኩ በሪፖርቱ ላይ እንደጠቀሰው 28 የኢትዮጵያ ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በአጭበርባሪዎች ገንዘባቸውን አጥተዋል ብሏል፡፡ የማጭበርበር ድርጊቶቹ የተፈጸሙት በሐሰተኛ የገንዘብ ኖቶች፣ በተሰረቁ የኤትኤም ማሽኖች፣ በሐሰተኛ ቼኮች፣ በሐሰተኛ የስልክ መልዕክት እና ተያያዥ መንገዶች አማካኝነት ነው፡፡ በዚህ ዓመት ባንኮች ያጡት ገንዘብ ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ300 ሚሊዮን ብር ጭማሪ እንዳሳየም በሪፖርቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡ በኢትዮጵያ በአጠቃላይ ካሉ 31 ባንኮች ውስጥ 28ቱ ሲጭበረበሩ የቀሪዎቹ ሶስት ባንኮች ማንነት ግን በሪፖርቱ ላይ አልተጠቀሰም፡፡ ባንኮች ከአነስተኛ የብድር እና ቁጠባ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ብድሮችን እየሰጡ…
Read More
የአፍሪካ እና መካከለኛው ምስራቅ ባንኮች ወደ የኢትዮጵያ ለመግባት እያሰቡ ነው ተባለ

የአፍሪካ እና መካከለኛው ምስራቅ ባንኮች ወደ የኢትዮጵያ ለመግባት እያሰቡ ነው ተባለ

ኢትዮጵያ እስካሁን በሯን ለውጭ ባንኮች ዝግ አድርጋ የቆየች ሲሆን አሁን ላይ የፖሊሲ ማሻሻያ ከተደረገ በኋላ የውጭ ሀገራት ባንኮች እንዲገቡ ምቹ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ መሆኑን ብሔራዊ ባንክ ከዚህ በፊት መግለጹ ይታወሳል፡፡ ለዚህም ሲባል የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ከአንድ ዓመት በፊት የተቋቋመ ሲሆን ዋና መቀመጫውን በደቡብ አፍሪካ ያደረገው ስታንዳርድ ባንክ በኢትዮጵያ ለመግባት ከስድስት ወራት በፊት አመልክቷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ የሞሮኮ፣ የኬንያ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ባንኮች በኢትዮጵያ የመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው መግለጻቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዋና ገዢ ማሞ ምህረቱ ተናግረዋ፡፡ ዋና ገዢው አክለውም የውጭ ሀገራት ባንኮች በኢትዮጵያ እንዲሰሩ የሚፈቅደው ህግ በቀጣዮቹ ሳምንታት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚጸድቅ ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ባንክ ፍቃድ ለማግኘት የሚፈልጉ…
Read More
ኢትዮጵያ ለአምስት ተቋማት የውጭ ምንዛሬ ቢሮ የስራ ፈቃድ ሰጠች

ኢትዮጵያ ለአምስት ተቋማት የውጭ ምንዛሬ ቢሮ የስራ ፈቃድ ሰጠች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለአምስት ባንክ ላልሆኑ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች የስራ ፈቃድ ሰጥቷል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ አገልግሎት እና ተደራሽነት ለማስፋት ከባንክ ጋር ከተያያዙ የውጭ ምንዛሬ ቢሮዎች በተጨማሪ ከባንክ ጋር ዝምድና የሌላቸው የግል የውጪ ምንዛሬ ቢሮዎችን ለመክፈት የሚያስችል የውጭ ምንዛሬ መመሪያ አውጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት አምስት የግል የውጭ ምንዛሬ ቢሮዎች መስፈርት በማሟላታቸው የስራ ፍቃድ እንደተሰጣቸው ባንኩ ገልጿል፡፡ ፈቃድ ከተሰጣቸው ድርጅቶች መካከል ዱግዳ ፊደሊቲ ኢንቨስትመንት፣ ኢትዮ ኢንዲፔንደንት፣ ግሎባል፣ ሮቡስት እና ዮጋ ፎርኤክስ የተባሉ የግል የውጪ ምንዛሬ ቢሮዎች ናቸው፡፡ በመሆኑም ቢሮዎቹ ሙሉ ተቀባይነት ያላቸው እና የውጭ ሀገር ጥሬ ገንዘቦችን በመግዛት እና በመሸጥ እንዲሁም ከባንኮች ጋር በመቀናጀት ለወጪ እና ገቢ ንግድ የሚውል የውጭ ምንዛሬ…
Read More
ኢትዮጵያ የመገበያያ ገንዘቧን በ31 በመቶ አዳከመች

ኢትዮጵያ የመገበያያ ገንዘቧን በ31 በመቶ አዳከመች

ኢትዮጵያ ከዛሬ ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ተመን ስርአት ተግባራዊ ማድረግ ጀምራለች፡፡ ኢትዮጵያ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ተመን ስርአት ተግባራዊ እንዲደረግ መወሰኗን ተከትሎ ባንኮች በዲሱን የምንዛሬ ተመን ዛሬ ተግባራዊ ማድረግ ጀምረዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ማሻሻውን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫው የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓቱ የውጭ ምንዛሪ ተመን በባንኮችና በደንበኞቻቸው መካከል ወደሚወስንበት የገበያ ሥርዓት መሸጋገሩን አስታውቋል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዛሬ ባወጣው የውጭ ምንዛሬ ተመን መሰረት አንድ የአሜሪካ ዶላር በ74.7364 ብር እየተገዛ በ76.2311 እየተሸጠ መሆኑን አስታውቋል። ኢትዮጵያ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ተመን ስርአት ተግባራዊነትን ተከትሎ በምንዛሬ ተመን በአንድ ዶላር ላይ በአማካይ የ18 ብር ጭማሪ ታይቷል። በኢትዮጵያ ንግድ…
Read More
መንግስት ብርን የማዳከም ፍላጎት እንደሌለው ገለጸ

መንግስት ብርን የማዳከም ፍላጎት እንደሌለው ገለጸ

ብሔራዊ ባንክ ሪፖርተር ጋዜጣ በሕዳር 23 እትሙ በውጭ ምንዛሬ ተመን ላይ ከፍተኛ ለውጥ ለማድረግ መታቀዱን በማስመልከት ያወጣው ዘገባ ሃሰተኛ መሆኑን ገልጿል፡፡ የሪፖርተር የአማርኛ ጋዜጣ ብሔራዊ ባንክ በውጭ ምንዛሪ ተመን ላይ በቅርብ ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ ለውጥ ለማድረግ ማቀዱን በማስመልከት ያወጣው ዘገባ ፈጽሞ ሐሰተኛና አሳሳች፣ ከጋዜጠኝነት ሥነ ምግባር ያፈነገጠ ድርጊት መሆኑን ባንኩ አስታውቋል፡፡ ባንኩ ይህን አስመልክቶ  ባወጣው መግለጫ የሪፖርተር የአማርኛ ጋዜጣ በህዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም እትሙ ብሔራዊ ባንክ ባለፈው ሳምንት የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለፓርላማ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ከአንድ የፓርላማ አባል ቀረበ ከተባለ አስተያየት ላይ ተነሥቶ ብሔራዊ ባንክ በውጭ ምንዛሪ ተመን ላይ…
Read More
ኢትዮጵያ ለአምስት የውጭ አገር ባንኮች ፍቃድ እንደምትሰጥ ገለጸች

ኢትዮጵያ ለአምስት የውጭ አገር ባንኮች ፍቃድ እንደምትሰጥ ገለጸች

አምስት የውጭ አገር ባንኮች ኢትዮጵያ ውስጥ ገብተው አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችላቸው ፈቃድ እንደሚሰጣቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ። አገር በቀል ባንኮች ከወዲሁ ከፍተኛ ዝግጅት ማድረግ እና ቀድሞ የነበራቸውን ስትራቴጂ መከለስ እንዳለባቸውም ባንኩ አሳስቧል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የገንዘብ ተቋማት ዘርፍ ምክትል ገዥ አቶ ሠለሞን ደስታ እንዳሉት የአገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋማትን ከማጠናከር ጎን ለጎንም የውጭ ባንኮችን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት እየተሰራ ነው። ‹‹ሥራውን አሁን እያጠናቀቅን ነው። አዋጁን የመከለስ ሥራውንም እያጠናቀቅን ነው:: ከለጋሾች አንዳንድ ግብዓቶችን እየጠየቅን ነው። በወራት ዕድሜ ለህዝብ እንደራሴዎች ይቀርባል:: ስለዚህ ስራው እየተፋጠነ ነው” ብለዋል አቶ ሠለሞን። በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት እስከ አምስት ለሚደርሱ የውጭ ባንኮች ፈቃድ ለመስጠት እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም አቶ ሠለሞን…
Read More
በኢትዮጵያ የጥሬ ገንዘብ እጥረት አጋጥማል መባሉን ብሔራዊ ባንክ አስተባበለ

በኢትዮጵያ የጥሬ ገንዘብ እጥረት አጋጥማል መባሉን ብሔራዊ ባንክ አስተባበለ

በኢትዮጵያ የጥሬ ገንዘብ እጥረት አጋጥማል መባሉን ብሔራዊ ባንክ አስተባብሏል። በኢትዮጵያ በተለይም የግል ባንኮች የጥሬ ገንዘብ እጥረት እንዳጋጠማቸው በተለያየ መልኩ ሲገለጹ ቆይቷል። የባንክ ደንበኞችም ለአገልግሎት ባመሩባቸው የግል ባንኮች የጥሬ ገንዘብ ሲጠይቁ እንዳልሰጧቸው በርካታ ሚዲያዎች ዘግበዋል። በስድስተኛው የምስራቅ አፍሪካ የፋይናንስ ጉባኤ እየተሰተፈ የሚገኘው ብሔራዊ ባንክ በዚህ ጥያቄ ዙሪያ ምላሽ ሰጥቷል። የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዢ አቶ ሰለሞን ደስታ እንዳሉት "በኢትዮጵያ በግል ባንኮች የጥሬ ገንዘብ እጥረት ገጥሟቸዋል እሚባለው መረጃ ሀሰት ነው" ብለዋል። የጥሬ ገንዘብ እጥረት ገጥሟቸዋል የተባሉት አምስት ባንኮች ናቸው መባሉን ሰምተናል ፣ "ነገር ግን በሶስት ባንኮች ላይ የተወሰነ የጥሬ ገንዘብ እጥረት ገጥሞ ነበር፣ ብሔራዊ ባንክ እና ሌሎች ተቋማት በወሰዷቸው ማስተካከያዎች አሁን ላይ ከአንድ…
Read More
ኢትዮጵያ ለአምስት የውጭ ባለሀብቶች የባንክ ፈቃድ ልትሰጥ መሆኑ ገለጸች

ኢትዮጵያ ለአምስት የውጭ ባለሀብቶች የባንክ ፈቃድ ልትሰጥ መሆኑ ገለጸች

። ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በባንክ ዘርፍ ለመሰማራት ፍላጎት ላላቸው የውጭ ባለሀብቶች አምስት የሚደርሱ የባንክ ፈቃድ ለመስጠት ማቀዷ ተገለጸ፡፡ የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ሰለሞን ደስታ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ከሦስት እስከ አምስት ለሚደርሱ በኢትዮጵያ በባንክ ዘርፉ መሰማራት ለሚፈልጉ የውጭ ባለሀብቶች የባንክ ፈቃድ እንደሚሰጥ መናገራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ ይህም የአገሪቱን የፋይናንስ ዘርፍ አገልግሎት ለውጭ ተፎካካሪዎች ክፍት ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡ እስካሁን የባንኩ ዘርፍ ለውጭ አገራት መዋዕለ ነዋይ አፍሳሾች ዝግ ሆኖ የቆየ ሲሆን፤ በቀጣይ አምስት ዓመታት ውስጥ ግን ለውጭ አገራት ተፎካካሪዎች ክፍት እንደሚደረግ ነው የተገለጸው፡፡ በተጨማሪም የውጭ ባለሀብቶች በኢንዱስትሪ ዘርፉም ከአገር ውስጥ ባለሀብቶች ጋር በጋራ የሚሰሩበት አማራጭ ሊኖር እንደሚችል በምክትል ገዥው በኩል ተጠቅሷል፡፡ የውጭ…
Read More