Forexservice

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የ1 ነጥብ ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ሊሰጥ መሆኑን አስታወቀ

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የ1 ነጥብ ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ሊሰጥ መሆኑን አስታወቀ

ዓለም ባንክ ከአንድ ወር በኋላ ለኢትዮጵያ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር በጀት ድጋፍ ሊያጸድቅ መሆኑን ገልጿል። አንድ የባንኩ ከፍተኛ ባለሙያ ሲናገሩ አዲስ ማለዳ ሰምታለች። የገንዘብ ሚኒስቴር ከሳምንት በፊት የ2019 ዓ.ም የበጀት ረቂቀን ለምክር ቤቱ ባቀረበበት ወቅት ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ መሆኑን ገልፆ የበጀት ጉድለቱ ከውጭ እርዳታ እና ሀገር ውስጥ በሚገኝባቸው ገቢ ይሸፈናል ማለቱ ይታወሳል። በዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ቢሮ የግሉ ዘርፍ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ብስራት ተሾመ እንደገለጹት ከሆነ ባንኩ ለኢትዮጵያ መንግስት የሚውል የአንድ ጊዜ የበጀት ድጋፍ በማዘጋጀት ላይ መሆኑን ተናግረዋል። ባለሙያው ይህን ያሉት ትናንት ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጋር ባዘጋጁት የውይይት መድረክ…
Read More
ብሔራዊ ባንክ አስመጪዎች እና ላኪዎች ያለ ባንክ ቅድመ እውቅና እቃ እንዲያዙ ፈቀደ

ብሔራዊ ባንክ አስመጪዎች እና ላኪዎች ያለ ባንክ ቅድመ እውቅና እቃ እንዲያዙ ፈቀደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ወደ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ተመን ሥርዓት እያደረገ ያለውን ሽግግር ለማጠናከር፣ የውጭ ምንዛሬ አስተዳደርን የሚያቀሉ አዳዲስ መመሪያዎችን ይፋ አድርጓል።ባንኩ ባወጣው መግለጫ ማሻሻያው የውጭ ምንዛሬ አስተዳደርን ይበልጥ ለማቅለልና በንግድ እንቅስቃሴ ላይ እንቅፋት የሆኑ የቢሮክራሲ ሰንሰለቶችን የሚያሳጥሩ ናቸው።በአዲሱ መመሪያ መሰረት የንግድ ባንኮች የውጭ ምንዛሬ ሂሳብ እና የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ሂሳብ  ላላቸው ደንበኞች የብድር ደብዳቤ እና የሰነድ መክፈያ ፈቃዶችን ያለ ብሔራዊ ባንክ ቅድመ ሁኔታ ማጽደቅ እንዲችሉ ሙሉ ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል።ይህ ማሻሻያ በተለይ በገቢና ወጪ ንግድ ላይ ለተሰማሩ ነጋዴዎች የጊዜና የቢሮክራሲ ጫናን ያቀላል ተብሎ ይጠበቃል።በተጨማሪም የውጭ ምንዛሬ ሂሳብ ያላቸው ተቋማት የባንኮችን ቅድመ ፈቃድ ሳይጠብቁ በሰነድ መክፈያ ስምምነት መሠረት የሸቀጦችን የጭነት ትዕዛዝ መስጠት…
Read More
ኢትዮጵያ ለአምስት ተቋማት የውጭ ምንዛሬ ቢሮ የስራ ፈቃድ ሰጠች

ኢትዮጵያ ለአምስት ተቋማት የውጭ ምንዛሬ ቢሮ የስራ ፈቃድ ሰጠች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለአምስት ባንክ ላልሆኑ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች የስራ ፈቃድ ሰጥቷል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ አገልግሎት እና ተደራሽነት ለማስፋት ከባንክ ጋር ከተያያዙ የውጭ ምንዛሬ ቢሮዎች በተጨማሪ ከባንክ ጋር ዝምድና የሌላቸው የግል የውጪ ምንዛሬ ቢሮዎችን ለመክፈት የሚያስችል የውጭ ምንዛሬ መመሪያ አውጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት አምስት የግል የውጭ ምንዛሬ ቢሮዎች መስፈርት በማሟላታቸው የስራ ፍቃድ እንደተሰጣቸው ባንኩ ገልጿል፡፡ ፈቃድ ከተሰጣቸው ድርጅቶች መካከል ዱግዳ ፊደሊቲ ኢንቨስትመንት፣ ኢትዮ ኢንዲፔንደንት፣ ግሎባል፣ ሮቡስት እና ዮጋ ፎርኤክስ የተባሉ የግል የውጪ ምንዛሬ ቢሮዎች ናቸው፡፡ በመሆኑም ቢሮዎቹ ሙሉ ተቀባይነት ያላቸው እና የውጭ ሀገር ጥሬ ገንዘቦችን በመግዛት እና በመሸጥ እንዲሁም ከባንኮች ጋር በመቀናጀት ለወጪ እና ገቢ ንግድ የሚውል የውጭ ምንዛሬ…
Read More