capitalmarket

ኢትዮጵያ የስቶክ ማርኬት ገበያን ከ50 ዓመት በኋላ ዳግም አስጀመረች

ኢትዮጵያ የስቶክ ማርኬት ገበያን ከ50 ዓመት በኋላ ዳግም አስጀመረች

ኢትዮጵያ በአጼ ሀይለስላሴ አስተዳድር ዘመን የስቶክ ግብይት የሚፈቅድ ስርዓት የነበራት ቢሆንም በደርግ ዘመን ተቋርጦ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ከ50 ዓመት በኋላ የስቶክ ግብይትን ዳግም ያስጀመረች ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ዛሬ ጥር 3 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ አስጀምረዋል፡፡ በዚህ የግብይት ስርዓት መሰረት ኩባንያዎች አክስዮኖቻቸውን በይፋ ለገዢዎች መሸጥ የጀመሩ ሲሆን ሸማቾች ደግሞ ለሚገዙት አክስዮን ዋስትና የሚሰጥ ተቋምም ወደ ስራ ገብቷል፡፡ ይህን የአክስዮን ግብይት የሚያሳልጡ ሁለት መንግስታዊ ተቋማት የተቋቋሙ ሲሆን የኢትዮጵያ ካፒታል ማርኬት እና የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ነዋዮች ገበያ ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ የስቶክ ግብይትን ከአንድ ዓመት በፊት የመጀመር እቅድ የነበራት ቢሆንም ዘግይቶ ተጀምሯል፡፡ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ስር 39 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው የመንግስት…
Read More
አራት ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ባንኮች በኢትዮጵያ ለመሰማራት መፈለጋቸው ተገለጸ

አራት ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ባንኮች በኢትዮጵያ ለመሰማራት መፈለጋቸው ተገለጸ

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዳይሬክተር ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) በተቋሙ ስራ ዙሪያ በሰጡት መግለጫ ከየካቲት 4 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ዘርፍ መሰማራት ለሚፈልጉ የሀገር ውስጥ እና ውጭ ተቋማት ፈቃድ መስጠት ይጀመራል ብለዋል። "እስካሁን ባለው ሂደት በርካታ ኢትዮጵያዊያን እና የውጭ ኩባንያዎች በኢንቨስትመንት ባንክ ለመሰማራት ፍላጎታቸውን አሳይተውናል" ያሉት ዳይሬክተሩ "ሶስት በዓለም አቀፍ ደረጃ ስም ያላቸው የውጭ ሀገር ኢንቨስትመንት ባንክ እና ሁለት የሀገር ውስጥ ተቋማት ፈቃዱን ለማግኘት እየጠየቁን ነው" ሲሉም ተናግረዋል። ይሁንና ዋና ዳይሬክተሩ በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ባንክ ለማቋቋም ፍላጎታቸውን የገለጹት ዓለም አቀፍ ባንኮች ስም ዝርዝር ከመናገር ተቆጥበዋል፡፡ ዋና መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ ያደረገው እና በበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ቅርንጫፍ ያለው ስታንደርድ ባንክ ባሳለፍነው…
Read More