01
Sep
በአሁኑ ወቅት በካፒታል ገበያ ሥር በተለያዩ ዘርፎች አገልግሎት ለመስጠት 10 ተቋማት የፈቃድ ማመልከቻ አስገብተው እየተጠባበቁ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን አስታውቋል። በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የምዝገባና ፈቃድ አሰጣጥ ኃላፊ አቶ እንድሪስ ሰልማን፤ በኢትዮጵያ ያለው የካፒታል ገበያ ገና በማደግ ላይ የሚገኝ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም ከጊዜ ወደጊዜ ፍላጎቱ እየጨመረ እንደሚመጣ ገልጸው፤ ያንን ፍላጎት ለመሙላት የሚያስችል ተጨማሪ አገልግሎት ሰጪዎች ገበያውን ሊቀላቀሉ የሚችሉበት ዕድል እንዳለ ተናግረዋል። በዚህም ወደ 10 ተቋማት እንዲሁም በግለሰብ ደረጃ ደግሞ አንድ ሰው የኢንቨስትመንትና የሰነደ መዋዕለ ነዋይ አማካሪነትን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የፈቃድ ማመልከቻ በማስገባት እየተጠባበቁ እንደሚገኙ አስታውቀዋል። ያመለከተው አካል በሙሉ ፈቃድ ይሰጠዋል ማለት እንዳልሆነ የገለጹት ኃላፊው፤ "በተቀመጠው የፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ መስፈርት መሰረት…