ukethiopia

እንግሊዝ ለትግራይ ታጣቂዎች መልሶ ማቋቋሚያ 16 ሚሊዮን ፓውንድ እንደምትሰጥ ገለጸች

እንግሊዝ ለትግራይ ታጣቂዎች መልሶ ማቋቋሚያ 16 ሚሊዮን ፓውንድ እንደምትሰጥ ገለጸች

የብሪታኒያ የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር በኢትዮጵያ ጉብኝት በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ ብሪታንያ መንግሥት ለኢትዮጵያ የ23 ሚሊየን ፓውንድ ድጋፍ እንደምታደርግ አስታውቃለች፡፡ ከዚህ ውስጥ 16 ሚሊዮን ፓውንዱ በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ወቅት ከተሳተፉት ውስጥ የትግራይ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም የሚውል እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የእንግሊዝ መንግስት በኢትዮጵያ የጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ዘርፍን ለመደገፍ የሚውል እና ለሶስት አመታት የሚቆይ የ6 ነጥብ 9 ሚሊየን ፓውንድ ድጋፍ እንደሚያደርግም አስታውቋል፡፡ ድጋፉ ትግራይን ጨምሮ ለተለያዩ ክልሎች የሚውል ሲሆን 7000 የሚሆኑ ሴት ሰራተኞችን ህይወት ለማሻሻል እና የወጭ ንግድን 20 በመቶ ለማሳደግ ያለመ ነው ተብሏል። ኢትዮጵያ ለሁለት ዓመታት በተካሄደው በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የተሳተፉ ተዋጊዎችን ወደ ቀድሞ ህይወታቸው ለመመለስ በጀት በማሰባሰብ ለይ ስትሆን የአውሮፓ ህብረት 12 ሚሊዮን…
Read More
ብሪታንያ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ያለው ግጭቶች አሳስቦኛል አለች

ብሪታንያ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ያለው ግጭቶች አሳስቦኛል አለች

የዩናይትድ ኪንግደም ዓለም አቀፍ ልማት፣ ሴቶች እና እኩልነት ሚኒስትር አኔሌሴ ዶድስ በኢትዮጵያ ጉብኘት አድርገዋል፡፡ ሚኒስትሯ በአዲስ አበባ በነበራቸው የአንድ ቀን ጉብኝታቸው ከኢትዮያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ጋር እንደተወያዩ ተገልጿል፡፡ የዩኬ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉብኝቱን አስመልክቶ በድረገጹ ባወጣው መግለጫ ሀገሪቱ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ያሉት ግጭቶች እንዳሳሰቡት አስታውቋል፡፡ መግለጫው አክሎም በሁለቱ ክልሎች ያሉ ግጭቶች ንጹሃን እየጎዱ ነው ያለ ሲሆን የግጭቱ ሁሉም ተሳታፊዎች አለመግባባቶቻቸውን በውይይት እንዲፈቱም ጥሪ አቅርቧል፡፡ ዩኬም ለኢትዮጵያ ሰላም፣ ደህንነት እና ኢኮኖሚ ድጋፍ ማድረግ እንደምትፈልግ ሚኒስትሯ ከአምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ጋር በነበራቸው ውይይት ወቅት መነሳቱም በመግለጫው ላይ ተጠቅሷል፡፡ ዩኬ የዓለም አቀፍ ልማት እኩልነት እና ሴቶች ሚኒስትርን ወደ ኢትዮያ የላከችው…
Read More