Netprofit

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 80 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማስመዝገቡን ገለጸ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 80 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማስመዝገቡን ገለጸ

መንግስታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተያዘው በጀት ዓመት 80 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታውቋል። የባንኩ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ እንደገለጹት፣ የተገኘው ትርፍ ባንኩ ባለፉት ጊዜያት ካጋጥሙት የህልውና አደጋ መውጣቱን ያሳያል ብለዋል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም ባንኩ ከስድስት ዓመታት በፊት ከነበረበት ችግር ወጥቶ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ደረጃ ቀዳሚ ከሚባሉ ጠንካራ ባንኮች ተርታ መሰለፉንም ተናግረዋል። ባንኩ ለደረሰበት ከፍተኛ የትርፍ መጠን በዋናነት ለግል ዘርፉ የሰጠው ትኩረት፣ የተበላሸ ብድር መጠን መቀነሱ እና የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎት መስፋፋትን በምክንያትነት አንስተዋል። ባንኩ እየተጠናቀቀ ባለው የዘንድሮው በጀት ዓመት 648 ቢሊዮን ብር አዲስ ብድር እንደሰጠም ፕሬዝዳንቱ አንስተዋል። ከተሰጠው ብድር ውስጥም 90 በመቶ የሚሆነውን ወይም 588 ቢሊዮን ብር ለግል ዘርፍ መቅረቡም ተገልጿል።…
Read More
አቢሲንያ ባንክ ሰባት ቢሊዮን ብር ማትረፉን ገለጸ

አቢሲንያ ባንክ ሰባት ቢሊዮን ብር ማትረፉን ገለጸ

አቢሲንያ ባንክ አጠቃላይ ሀብቱ ከ286 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን አስታውቋል። አቢሲንያ ባንክ በዛሬው ዕለት ዓመታዊ የባለአክስዮኖች 29ኛ መደበኛ እና 16ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤው አካሂዷል። በጉባኤው ላይ እ.ኤ.አ በ2024/25 የሒሳብ ዓመት ሪፖርት የቀረበ ሲሆን፤ የባንኩ አጠቃላይ ሀብት 286 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታውቋል፡፡ ይህም ካለፈው ዓመት አጠቃላይ ሀብት ማለትም ከ222 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ጋር ሲነጻጸር የ63 ነጥብ 9 ቢሊዮን ወይም የ28 ነጥብ 8 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን የአቢሲኒያ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር አቶ መኮንን ማንያዘዋል ገልጸዋል። ባለፈው የሒሳብ ዓመት የባንኩ ጠቅላላ ገቢው 39 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር መድረሱን የገለጹ ሲሆን፤ ውጤቱ ካለፈው ተመሳሳይ ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ11 ነጥብ 3 ቢሊዮን…
Read More