Jobsinethiopia

ከደላሎች ውጪ ሰራተኞችን ከቀጣሪዎች ጋር በቀጥታ የሚያገናኝ መተግበሪያ ተዘጋጀ

ከደላሎች ውጪ ሰራተኞችን ከቀጣሪዎች ጋር በቀጥታ የሚያገናኝ መተግበሪያ ተዘጋጀ

የቤት ውስጥ ሰራተኛን ጨምሮ የግል አገልግሎት ሰራተኞች እና አሰሪዎችን የሚያገናኝ፣ ደላላን የሚተካ መተግበሪያ እየተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። የግል አገልግሎት ቅጥር የሚባሉትን እንደ አትክልተኛ፣ የቤት ውስጥ ተንከባካቢ፣ የቤት ውስጥ አብሳይ (ሼፍ) እና ሌሎችም ዘርፎች የቅጥር ግንኙነት ከደላላ ጣልቃ-ገብነት የሚያላቅቅ መተግበሪያ እና አዲስ ደንብ እየተዘጋጀ እንደሆነ ተገለጸ። ዓለም አቀፍ የሥራ ድርጅት ኮንቬንሽን 189ን ታሳቢ አድርጎ የተዘጋጀው ደንብ ለፍትሕ ሚኒስቴር መቅረቡን እና በቅርቡ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር አስታውቋል። አንድ ዓመት አካባቢ ለሚፈጅ ጊዜ ግብዓት በማሰባሰብ እና ባለድርሻ አካላትን በማወያየት የተዘጋጀው ደንብ፣ የቤት ሠራተኞች መመዝገቢያ ሶፍትዌር ሲስተም እንዲኖረው የሚያስችል መተግበሪያ እየተዘጋጀለት እንደሆነ የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ…
Read More
ኢትዮጵያ 50 የኮንስትራክሽን ሰራተኞችን ወደ ጀርመን ልትልክ ነው

ኢትዮጵያ 50 የኮንስትራክሽን ሰራተኞችን ወደ ጀርመን ልትልክ ነው

በኮንስትራክሽን ሥራ የሚሰማሩ 50 ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች ወደ ጀርመን ከማቅናታቸው በፊት አዲስ አበባ ባለው የጀርመን ኢንስቲትዩት ተጨማሪ ስልጠናዎችን በመውሰድ ላይ ናቸው፡፡ በኮንስትራክሽን ሥራ ለመሠማራት የሚያበቃቸውን ሥልጠና ያጠናቀቁ የመጀመሪያው ዙር ባለሙያዎች ወደ ጀርመን እንደሚሄዱ ተገልጿል፡፡ ሥልጠናቸውንና ፈተናቸውን አጠናቀው ጀርመን ከሚገኙ አሠሪዎቻቸው ጋር የሥራ ውል የተፈራረሙት የመጀመሪያዎቹ ተጓዦች በመጪው አንድ ወር ውስጥ  ጉዞ እንደሚያደርጉ ተሰምቷል።  ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በሲቭል ኢንጂነሪንግ፣ በኮንስትራክሽን ማናጅሜንት ቴክኖሎጂ፣ በአርክቴክቸርና መሰል ሙያዎች የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ምሩቃን ወጣቶች ጎኤቴ በመባል በሚታወቀው የጀርመን ባህልና ቋንቋ ኢንስቲትዩት ሥልጠናቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ሥምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ንጉሡ ጥላሁን እንዳሉት ሥልጠናው ከሦሥት ዓመት በፊት በቀድሞው ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር…
Read More