jobopportunity

ኢትዮጵያ 50 የኮንስትራክሽን ሰራተኞችን ወደ ጀርመን ልትልክ ነው

ኢትዮጵያ 50 የኮንስትራክሽን ሰራተኞችን ወደ ጀርመን ልትልክ ነው

በኮንስትራክሽን ሥራ የሚሰማሩ 50 ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች ወደ ጀርመን ከማቅናታቸው በፊት አዲስ አበባ ባለው የጀርመን ኢንስቲትዩት ተጨማሪ ስልጠናዎችን በመውሰድ ላይ ናቸው፡፡ በኮንስትራክሽን ሥራ ለመሠማራት የሚያበቃቸውን ሥልጠና ያጠናቀቁ የመጀመሪያው ዙር ባለሙያዎች ወደ ጀርመን እንደሚሄዱ ተገልጿል፡፡ ሥልጠናቸውንና ፈተናቸውን አጠናቀው ጀርመን ከሚገኙ አሠሪዎቻቸው ጋር የሥራ ውል የተፈራረሙት የመጀመሪያዎቹ ተጓዦች በመጪው አንድ ወር ውስጥ  ጉዞ እንደሚያደርጉ ተሰምቷል።  ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በሲቭል ኢንጂነሪንግ፣ በኮንስትራክሽን ማናጅሜንት ቴክኖሎጂ፣ በአርክቴክቸርና መሰል ሙያዎች የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ምሩቃን ወጣቶች ጎኤቴ በመባል በሚታወቀው የጀርመን ባህልና ቋንቋ ኢንስቲትዩት ሥልጠናቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ሥምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ንጉሡ ጥላሁን እንዳሉት ሥልጠናው ከሦሥት ዓመት በፊት በቀድሞው ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር…
Read More
ከፊሊፒንስ ጋር የተጣላችው ኩዌት ኢትዮጵያዊያንን እንደምትቀጥር ገለጸች

ከፊሊፒንስ ጋር የተጣላችው ኩዌት ኢትዮጵያዊያንን እንደምትቀጥር ገለጸች

በነዳጅ የበለጸገችው የመካከለኛው መስራቅ ሀገር ኩዌት የሦስት ወራት አስገዳጅ ስልጠና የወስዱ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን ለመቀበል ከመንግሥት ጋር ስምምነት ላይ መድረሷ ተገልጿል። በኢትዮጵያ እና ኩዌት መንግሥታት በኩል መግባባት ላይ መደረሱን ተከትሎም፤ በጥቂት ቀናት ውስጥ የጋራ የሥራ ስምምነት እንደሚፈረም አረብ ታይምስ ዘግቧል። ከስምምነቱ በኋላ በኢትዮጵያ የሚገኙ 600 የሚሆኑ የሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች የሰው ኃይል በማቅረብ ይሰራሉም ተብሏል፡፡ ኢትዮጵያን ሰራተኞች ቢያንስ ብቃቱ ከተረጋገጠ ተቋም የ3 ወር ስልጠና መውሰድ በግዴታ ተጥሎባቸዋል፡፡ ኩዌት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን የቤት ሰራተኞች የምታገኘው ከፊሊፒንስ ሲሆን፤ በኹለቱ አገራት መካከል የተፈጠረውን ውጥረት ተከትሎ አገሪቱ የሰራተኛ እጥረት በማጋጠሙ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን ለመቀበል ማቀዷ ተገልጿል። የኢትዮጵያ መንግሥት ከኩዌት መንግሥት ጋር በተስማሙት መሰረት፤ አንድ ሰራተኛ በወር 90…
Read More