Jobssearch

ኢትዮጵያ በሶስት ወራት ውስጥ ከ87 ሺህ በላይ ዜጎችን ወደ ውጭ ሀገራት መላኳ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በሶስት ወራት ውስጥ ከ87 ሺህ በላይ ዜጎችን ወደ ውጭ ሀገራት መላኳ ተገለጸ

የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል የሶስት ወራት እቅድ አፈጻጸማቸውን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበዋል፡፡ ሚኒስትሯ በዚህ ወቅት እንደገለጹት ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ 140 ሺህ ኢትዮጵያዊያንን ወደ ውጭ ሀገራት ለስራ ለመላክ ታቅዶ ነበር ብለዋል፡፡ የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በዘንድሮ በጀት ዓመት 700 ሺህ ኢትዮጵያውያንን ወደ ውጭ ሀገራት ለስራ ለመላክ እቅድ እንደነበረውም ሚኒስትሯ አክለዋል፡፡ ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት 332 ሺህ ኢትዮጵያዊያን ወደ ውጭ ሀገራት ለስራ መላካቸውም ተገልጿል። ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች የተላከባቸው ሀገራት ስድስት የመካከለኛው ምስራቅ እና ሁለት የአውሮፓ ሀገራት ናቸው።  ሀገራቱ “የሰለጠኑ” እና “በከፊል የሰለጠኑ” ሰራተኞችን ከኢትዮጵያ እንደሚፈልጉ የጠቆሙት ሙፈሪያት፤ በጤና፣ በምህንድስና፣ በአርክቴክቸር፣ በሆቴል እና መስተንግዶ ዘርፎች፣ በኤሌክትሪክ እና ቧንቧ ስራዎች እንደዚሁም…
Read More
ኢትዮጵያ 50 የኮንስትራክሽን ሰራተኞችን ወደ ጀርመን ልትልክ ነው

ኢትዮጵያ 50 የኮንስትራክሽን ሰራተኞችን ወደ ጀርመን ልትልክ ነው

በኮንስትራክሽን ሥራ የሚሰማሩ 50 ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች ወደ ጀርመን ከማቅናታቸው በፊት አዲስ አበባ ባለው የጀርመን ኢንስቲትዩት ተጨማሪ ስልጠናዎችን በመውሰድ ላይ ናቸው፡፡ በኮንስትራክሽን ሥራ ለመሠማራት የሚያበቃቸውን ሥልጠና ያጠናቀቁ የመጀመሪያው ዙር ባለሙያዎች ወደ ጀርመን እንደሚሄዱ ተገልጿል፡፡ ሥልጠናቸውንና ፈተናቸውን አጠናቀው ጀርመን ከሚገኙ አሠሪዎቻቸው ጋር የሥራ ውል የተፈራረሙት የመጀመሪያዎቹ ተጓዦች በመጪው አንድ ወር ውስጥ  ጉዞ እንደሚያደርጉ ተሰምቷል።  ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በሲቭል ኢንጂነሪንግ፣ በኮንስትራክሽን ማናጅሜንት ቴክኖሎጂ፣ በአርክቴክቸርና መሰል ሙያዎች የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ምሩቃን ወጣቶች ጎኤቴ በመባል በሚታወቀው የጀርመን ባህልና ቋንቋ ኢንስቲትዩት ሥልጠናቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ሥምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ንጉሡ ጥላሁን እንዳሉት ሥልጠናው ከሦሥት ዓመት በፊት በቀድሞው ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር…
Read More