Planting

ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞችን ተከለች

ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞችን ተከለች

ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞችን ተከለች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ "በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞች ተተክሏል" ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በዛሬው እለት 567 ሚሊዮን ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል። በአንድ ቀን 500ሺ ችግኝ የመትከል ዘመቻ አማካኝነት በሀገሪቱ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ችግኝ ሲተክሉ የሚያሳዩ ፎቶዎች እና ቪዲዮዎች ተለቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የችግኝ ተከላው" ለኢትዮጵያ ትልቅ ስኬት" ነው ሲሉ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በዚህ አመት ብቻ ከካርቦን ሽያጭ 52 ሚሊዮን ዶላር ማግኘቷን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የችግኝ ተከላው ስራ በዚሁ ከቀጠለ ከካርቦን ሽያጭ የምታገኘው ገቢ በእጥፍ እንደሚጨምር ገልጸዋል። ይሁንና በአንድ ጀምበር ተተከለ የተባለው የችግኝ መጠን በትክክል ስለመተከሉ በገለልታኛ አካል አልተረጋገጠም።
Read More