Who

ኢትዮጵያ የማርበርግ ወረርሽኝን መቆጣጠሯን አስታወቀች

ኢትዮጵያ የማርበርግ ወረርሽኝን መቆጣጠሯን አስታወቀች

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተከስቶ የነበረው የማርበርግ ቫይረስ (Marburg Viral Disease) ወረርሽኝ ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር መቻሉን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። ሚኒስቴሩ ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመሆን ፣ ወረርሽኙ ለመጀመሪያ ጊዜ መከሰቱ በይፋ ከተነገረበት ከሕዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሽታውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ሰፊ ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል። በወረርሽኙ ወቅት በአጠቃላይ ለ3 ሺህ 800 ሰዎች የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ ቫይረሱ የተገኘባቸው 14 ሰዎች ነበሩ። ከታካሚዎቹ መካከል ዘጠኙ በበሽታው ምክንያት ሕይወታቸው ሲያልፍ፣ አምስቱ ደግሞ ተገቢውን ሕክምና አግኝተው ማገገም መቻላቸው ይታወቃል። ወረርሽኙን በአጭር ጊዜ ለመቆጣጠር እንዲቻል የክትትልና ምላሽ ስርዓት ተዘርግቶ ሲሰራ መቆየቱን የገለጸው ሚኒስቴሩ በተለይም ከ4 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ተጓዦች በመውጫና…
Read More
ዶክተር ቴድሮስ አድሀኖም በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገለጹ

ዶክተር ቴድሮስ አድሀኖም በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገለጹ

ዶክተር ቴድሮስ አድሀኖም በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገለጹ። የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሀኖም በትዊተር ገጻቸው ላይ እንዳሉት በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ሁለተኛው ሰፊ የህዝብ ብዛት ያለው የአማራ ክልል ዋና ዋና መተላለፊያ መንገዶች መዘጋት የሰብዓዊ ድጋፍ ስራዎችን ያደናቅፋል ሲሉም ዶክተር ቴድሮስ ተናግረዋል። በክልሉ የኢንተርኔት መዘጋት የኮሙንኬሽን ስራውን አስቸጋሪ እንዳደረገውም ዳይሬክተሩ አክለዋል። ግጭቶች በህዝብ ጤና ላይ ወዲያውኑ ጉዳት ያደርሳሉ ያሉት ዶክተር ቴድሮስ ለተራዘመ የጤና እክሎች ይዳርጋሉም ብለዋል። በመሆኑም በአማራ ክልል የጤና መሰረተ ልማቶች ከጉዳት እንዲጠበቁ፣ የዓለም ጤና ድርጅት እና አጋሮች ስራቸውን እንደሚቀጥሉም ዶክተር ቴድሮስ አሳስበዋል። በተያያዘ ዜና በአማራ ክልል የተከሰተውን ግጭት ለመፍታት፤ በሌሎች የኢትዮጵያ ክልሎች የተጀመሩ…
Read More
ዶናልድ ትራምፕ ቻይና 50 ትሪሊዮን ዶላር ካሳ እንድትከፍል ጠየቁ

ዶናልድ ትራምፕ ቻይና 50 ትሪሊዮን ዶላር ካሳ እንድትከፍል ጠየቁ

ዶናልድ ትራምፕ ቻይና 50 ትሪሊዮን ዶላር ካሳ እንድትከፍል ጠየቁ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቻይና 50 ትሪሊዮን ዶላር ካሳ ልትከፍል ይገባል ብለዋል። የኮሮና ቫይረስ ከቻይና ውሀን ቤተ ሙከራ ውስጥ ማምለጡን የሚናገሩት ትራምፕ ቫይረሱ በአሜሪካ ላይ ላደረሰው ጉዳት ቻይና ካሳ እንድትከፍል ጠይቀዋል ሲል ዴይሊ ሜይል ዘግቧል። አሜሪካ በተደጋጋሚ የኮሮና ቫይረስ ከቻይና ቤተ ሙከራ አምልጧል በሚል ስትናገር የሚሰማ ሲሆን ቻይና ግን ይህን ክስ ውድቅ አድርጋለች። የኮረና ቫይረስ በዓለም ላይ ከስድስት ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ሲገድል አሜሪካ፣ ብራዚል እና ሕንድ ብዙ ዜጎቻቸውን በሞት ያጡ ሀገራት ናቸው።
Read More