industryparks

ኢትዮጵያ 10 የኢንዱስትሪ ፓርኮቿን ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞንነት አሳደገች

ኢትዮጵያ 10 የኢንዱስትሪ ፓርኮቿን ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞንነት አሳደገች

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስፈላጊዉን መስፈርት አሟልተዋል ያላቸዉን 10 ኢንዱስትሪ ፓርኮችን ወደ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን እንዲያድጉ መወሰኑ ተገልጿል። የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በበኩሉ እንዳስታወቀው በስሩ ከሚያስተዳድራቸው 13 ኢንዱስትሪ ፓርኮችና የድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና መካከል 10ሩ ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ማደጋቸውን አሳዉቋል። አሁን በስራ ላይ ካሉ 13 ኢንዱስትሪ ፓርኮች መካከል ወደ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ያደጉት አዳማ ባህርዳር ፣ ቦሌ ለሚ ፣ ደብረ ብረሃን እና ሀዋሳ ፣ ጅማ ፣ ቂሊንጦ ፣ ኮምቦልቻ ፣ መቀሌ እና ሰመራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መሆናቸው ታዉቋል። በኢትዮጵያ የሚገኙ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ለማሳደግ አዋጅ ቁጥር 1322/2016 በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቆ ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል። ኢንዱስትሪ ፓርኮቹ…
Read More
ኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ፓርክ ምርቶች ለሀገር ውስጥ ገበያ እንዲቀርቡ ፈቀደች

ኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ፓርክ ምርቶች ለሀገር ውስጥ ገበያ እንዲቀርቡ ፈቀደች

ኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን እና የውጪ ንግድን ለማሳደግ በሚል ነበር ኢንዱስትሪ ፓርኮችን የገነባችው፡፡ አሁን ላይ 13 የኢንዱስትሪ ፓርኮች ያሏት ኢትዮጵያ ፓርኮች የምርታቸውን 50 በመቶ ለሀገር ውስጥ ገበያ እንዲያቀርቡ ፈቅዳለች፡፡ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚሰሩ ኩባንያዎች 50 በመቶ ምርታቸውን ለሀገር ውስጥ ገበያ እንዲያቀርቡ መፈቀዱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታውቋል። በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚሰሩ ኩባንያዎች ምርታቸውን ሙሉ በሙሉ ለውጭ ገበያ እንጂ ለሀገር ውስጥ ማቅረብ ሳይፈቀድላቸው መቆየቱን የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን ገልጸዋል። ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች ተጽዕኖ ሥር የነበሩ ባለሃብቶችን ለማበረታታት በፓርኮች ውስጥ የሚሰሩ ኩባንያዎች 50 በመቶ ምርታቸውን ለሀገር ውስጥ ገበያ እንዲያቀርቡ በአዋጅ መፈቀዱን አስታውቀዋል። ከሁለት ዓመት በፊት በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት መቀስቀሱን ተከትሎ አሜሪካ…
Read More
ከኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች 51 ባለሀብቶች ለቀው መውጣታቸው ተገለጸ

ከኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች 51 ባለሀብቶች ለቀው መውጣታቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ የተሰማሩ የውጭ ሀገራት ኢንቨስተሮች በሙስና ምክንያት ከሚሰሩባቸው የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለቀው እየወጡ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የበጀት ዓመቱን ዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል፡፡ በኢትዮጵያ በተለያዩ የምርት ዘርፎች የተሰማሩ የውጭ ሀገራት ኩባንያዎች ከመንግስት ተቋማት መሪዎች እና ባለሙያዎች በሚጠየቁ ክፍያ ምክንያት መማረራቸው ተገልጿል፡፡ ምክር ቤቱ የኢንቨስትመንት ኮሚሽኑንን ሪፖርት በገመገመበት ወቅት እንደገለጸው በኦሮሚያ ክልል ዱከም ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው ኢስተርን ኢንዱስትሪ ፓርክ ያሉ ኩባንያዎች ቅሬታ እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡ የምክር ቤቱ አባላት በዚህ ኢንዱስትሪ ፓርክ ባደረጉት ምልከታ ኢንቨስተሮች የሚጠይቋቸውን ከትንሽ እስከ ትልቅ አገልግሎቶች በገንዘብ እየገዙ ነው ብለዋል፡፡ እንዲሁም በፓርኩ ላይ የባለቤትነት ስሜት ባለመኖሩ ፓርኮች ውስጥ እየገቡ ዘረፋ እየተፈጸባቸው መሆኑን የምክር…
Read More