03
Apr
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅን አጽድቋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ላይ ከተወያየ በኋላ አጽድቋል። በምክር ቤቱ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ተስፋዬ በልጂጌ ለምክር ቤቱ አባላት በሰጡት ማብራሪያ፤ መንገግስት የዜጎች መሰረታዊ ፍላጎት የሆነውን የመኖሪያ ቤት አቅርቦት ለማሻሻል የተለያዩ ጥረቶች እያደረገ ቢሆንም፤ ከመኖሪያ ቤት ፍላጎት ጋር ሊጣጣም አልቻለም ብለዋል። አቶ ተስፋዬ አክለውም ፤ በኢትዮጵያ የተጋነኑ እና ከተከራዮች የመክፈል አቅም በላይ የሆነ የቤት ኪራይ ጭማሪዎች በከተሞች እንዳሉ ተናገረዋል፡፡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ በተለይ በዝቅተኛ ገቢ የሚተዳደሩ የከተማ ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ቅሬታ እያስነሳ እና ዜጎችም ተረጋግተው ኑሯቸውን…