Realstateinethiopia

ኖህ ሪል ኢስቴት 754 መኖሪያ ቤቶችን አስመረቀ

ኖህ ሪል ኢስቴት 754 መኖሪያ ቤቶችን አስመረቀ

ኖህ ሪል እስቴት አስረኛ ዓመቱን 754 አዳዲስ መኖሪያ ቤቶችን በማስረከብ አክብሯል ኖህ ሪል ስቴት ኃ/የተ/የግ/ማህበር 10ኛ አመት የምስረታ በአሉን  754 አዳዲስ የመኖሪያ ቤቶችን ገንብቶ በማስረከብ አክብሯል። በኢትዮጵያ የከተማ ልማት ከፍተኛ እድገት አበርክቶ ያለው ኖህ ሪል ኢስቴት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ደንበኞቹና የሚዲያ አባላት ጋር አክብሯል። ኖህ ሪል እስቴት ባለፉት አስርት አመታት 8,000 በላይ ለሆኑ ቤተሰቦች በከፍተኛ ጥራት የተገነቡ ቤቶችን በታማኝነት፣ በሰዐቱ እና በቃሉ መሰረት አስረክቧል። ይህ ጉዞ ኩባንያውን በኢትዮጵያ የቤቶች ልማት ዘርፍ ቁልፍ ተዋናይ ሆኖ እንዲቀጥል አስችሎታል።  ለአገራዊ የልማት ግቦች ስኬትም ትልቅ አስተዋፅዖ እያደረገ ይገኛል። የኖህ ሪል ኢስቴት ዋና ስራ አስፈፃሚ ንፁህ አዉግቸዉ “በዛሬው ዕለት በኖህ ግሪን ፓርክ ሳይት አዲስ የተገነባውን …
Read More
በአዲስ አበባ 100 ሺህ ቤቶችን በአንድ ዓመት ውስጥ ለመገንባት ስምምነት ተፈረመ

በአዲስ አበባ 100 ሺህ ቤቶችን በአንድ ዓመት ውስጥ ለመገንባት ስምምነት ተፈረመ

የቤቶቹ ግንባታ በ68 የሪል ኢስቴት አልሚዎች እንደሚገነባ የተገለጸ ሲሆን መንግሥት መሬት በነጻ ለማቅረብ ተስማምቷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመንግሥትና በግል አጋርነት ፕሮጀክት አማካይነት በመረጣቸው ሪል ስቴት አልሚዎች፣ ከግማሽ ትሪሊዮን ብር በላይ ወጪ የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ ሊካሄድ ነው ተብሏል። በዚህ ፕሮግራም ሥር እንዲሳተፉ 68 ሪል ስቴት አልሚዎችን የመረጠ ሲሆን፤ አልሚዎቹም በተቀመጠው 70/30 አጋርነት መሠረት ከከተማ አስተዳደሩ ጋር ተጣምረው ግንባታውን ለማካሄድ ውል መግባታቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። ከእነዚህም አልሚዎች ውስጥ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ፣ ኦቪድ ግሩፕ፣ ፍሊንትስቶን ሆምስ፣ እንይ ኮንስትራክሽን፣ ጊፍት ሪል ስቴትና ሌሎችም ይገኙበታል። የከተማ አስተዳደሩ የቤቶቹን ግንባታ ለማካሄድ የሚያስፈልገውን መሬት ከሊዝ ነፃ ማቅረብና መሠረተ ልማቶችን የማሟላት ኃላፊነት አለበት ተብሏል። የሪል ስቴድ ድርጅቶች…
Read More
ፍሊንትስቶን ሪልስቴት 10 ሚሊዮን አክሲዮኖችን ለሽያጭ አቀረበ

ፍሊንትስቶን ሪልስቴት 10 ሚሊዮን አክሲዮኖችን ለሽያጭ አቀረበ

ደርጅቱ በቀጣዮቹ አምስት አመታት ውስጥ 10 ሺህ ቤቶችን እንደሚገነባ አስታውቋል፡፡ ከ30 አመታት በላይ በመኖሪያ ቤት ግንባታ እና በኮንስትራክሽን ዘርፉ የተሰማራዉ ፍሊንትስቶን ሪልስቴት 10 ሚሊዮን አክሲዮኖችን ለገበያ ማቅረቡን አስታዉቋል። የፍሊንትስቶን መስራችና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ጸደቀ ይሁኔ እንደተናገሩት ከ20 ሺህ ብር ጀምሮ እስከ 2 ሚሊዮን ብር ድረስ ዋጋ ያላቸዉን አክሲዮኖች ለሽያጭ መቅረባቸዉን ተናግረዋል። የአንዱ አክሲዮን ዋጋም 1 ሺህ ብር መሆኑን ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል። ከሚቀጥለው ሐምሌ ጀምሮ ሽያጩ ይጀመራል የተባለ ሲሆን ባለ አክሲዮኖች ባላቸዉ የድርሻ መጠን ተሰልቶ አልያም በፍላጎታቸዉ ተጨማሪ ገንዘብ ከፍለዉ የቤት ባለቤት መሆን የሚችሉበት እድል መመቻቸቱን ገልጸዋል፡፡ በዋነኛነት አክሲዮን ሽያጩ ያስፈለገዉ ተጨማሪ ካፒታል ለማግኘት ፣ ድርጅቱን ከ አምስት ሰዎች የሽርክና ባለቤትነት…
Read More