31
Aug
የሲንጋፖር የወደብ ባለስልጣን በኢትዮጵያ በሎጀስቲክስ ኢንቨስትመንት እንዲሰማራ ጥሪ ቀረበ ዓለም አቀፍ የእስያ ኩባንያዎችን ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ እና ኢንቨስት እንዲያደርጉ ለማሳመን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ሲንጋፖርን በመጎብኘት ላይ ናቸው፡፡ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ ጋር በመሆን ሲንጋፖር የሚገኘውን የሲንጋፖር የወደብ ባለስልጣን ጎብኝተዋል። ሁለቱ የኢንቨስትመንት አመራሮች ከሲንጋፖር ወደብ ባለስልጣን ኃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል። በውይይቱም የሲንጋፖር የወደብ ባለስልጣን በኢትዮጵያ በሎጀስቲክስ ኢንቨስትመንት እንዲሰማራ ጠይቀዋል። የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ፣ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ከፍተኛ ፍላጎት ገልፀው ባለስልጣኑ በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት የሚሰማራበትንና ልምድ የሚያካፍልበት መንገድ እንዲኖር ጥሪ አቅርበዋል። የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ በበኩላቸው ፈጣን…