remedial

ስድስት ዩንቨርሲቲዎች የሬሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎችን እንደማይቀበሉ ተገለጸ

ስድስት ዩንቨርሲቲዎች የሬሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎችን እንደማይቀበሉ ተገለጸ

ትምህርት ሚኒስቴር በ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ከግማሽ በላይ ውጤት ያላመጡ ተማሪዎችን እንደሚመድብ ገልጿል፡፡ ይሁንና ስድስት የመንግስት ዩንቨርሲቲዎች የሬሚዲያል ተማሪዎችን እንደማይቀበሉ አስታውቋል፡፡ የሬሚዲያል ተማሪዎችን ከማይቀበሉ ዩንቨርሲቲዎች መካከልም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ፣ አርሲ ዩኒቨርሲቲ እና ኮተቤ የትምህርት ዪኒቨርሲቲዎች ናቸው፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር እነዚህ ዩንቨርሲቲዎች ለምን የሬሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎችን እንደማይቀበሉ ምክንያታቸውን አልጠቀሰም፡፡ በ2015 የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተናን ከወሰዱ 845 ሺሕ 099 ተማሪዎች ውስጥ፤ 817 ሺሕ 838 ተማሪዎች ከ50 በመቶ በታች የሆነ ውጤት ማምጣታቸው ይታወሳል፡፡ የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በሰጡት መግለጫ ከአጠቃላይ 845 ሺሕ 099 ተፈታኞች ውስጥ…
Read More