humanrights

መንግሥት የጎዳና ተዳዳሪዎችን በግዴታ ወደ ማጎሪያ ስፍራ እያስገባ መሆኑን ኢሰመኮ ገለጸ

መንግሥት የጎዳና ተዳዳሪዎችን በግዴታ ወደ ማጎሪያ ስፍራ እያስገባ መሆኑን ኢሰመኮ ገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በጎዳና ላይ ያሉ ሰዎችን ያለፈቃዳቸው መያዝና ወደ ማቆያ ማዕከላት ማስገባት የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን ስለሚያስከትል ሊቆም ይገባል ሲል  አሳስቧል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ በሚከበሩ ሕዝባዊና ሃይማኖታዊ በዓላት፣ ዓለም አቀፋዊና አህጉራዊ ጉባኤዎች እንዲሁም ከሌሎች ተመሳሳይ ኹነቶች ጋር በተያያዘ ውሎና አዳራቸውን በጎዳና ላይ ያደረጉ ሰዎችን በኃይል በማንሳት በአንድ ስፍራ እንዲቆዩ የማድረግ ስራ በተደጋጋሚ እንደሚከናወን መግለጫው አመላክቷል፡፡ ኢሰመኮ በታኅሣሥ ወር 2017 ዓ.ም ባደረጋቸው ክትትሎች በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ “ቃሊቲ አካባቢ” ተብሎ በሚጠራው የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ አካባቢ ሰፊ መጋዘን ውስጥ ከጎዳና ላይ የተነሱ በርካታ ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡ ወደ ማቆያው ከገቡት ሰዎች መካከል በማዕከሉ ከመቆየት እና የእርሻ ሥራ ከመሥራት እንዲመርጡ በማድረግ፤ የእርሻ…
Read More
አምንስቲ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ ያስተላለፈችውን እገዳ ተቃወመ

አምንስቲ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ ያስተላለፈችውን እገዳ ተቃወመ

የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረስበ ድርጅቶች ባለስልጣን በሲቪል ማህበረሰብ ስራዎች ዙሪያ የተሰማሩ ድርጅቶችን ማሸጉ ይታወሳል፡፡ ከታገዱት ድርጅቶች መካከልም “የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል” (CARD) “ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች ኢትዮጵያ” (AHRE) እና ሌሎችም ይገኙበታል። ባለሥልጣኑ ለድርጅቶቹን ያገደው በፖለቲካ ጉዳዮች ዙሪያ ጣልቃ ገብተዋል በሚል ነበር፡፡ አለም አቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተቆርቋሪው አምነስቲ ኢንተርናሽናል የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት በሦስት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ የጣለውን እገዳ አውግዟል፡፡ የመብቶች እና የዲሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ)፣ ስብስብ ለሰብዓዊ መብቶች በኢትዮጵያ እና የሕግ ባለሙያዎች ለሰብዓዊ መብቶች የተሰኙት ድርጅቶች ላይ የተጣለው እገዳ በሲቪል ማኅበረሰቡ ምኅዳር ላይ የተቃጣው አፈና እየጨመረ ስለመሆኑ ማሳያ ነው ሲልም አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው መግለጫ ላይ ጠቅሷል። የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምሥራቅ እና ደቡባዊ…
Read More
መንግሥት ሁለት የሰብአዊ መብት ድርጅቶችን አገደ

መንግሥት ሁለት የሰብአዊ መብት ድርጅቶችን አገደ

የሲቪል ማህበረስበ ድርጅቶች ባለስልጣን በሰብአዊ መብት ሥራዎች ታዋቂ የሆኑ ድርጅቶችን እንዳሸገ ተገልጿል፡፡ ከታገዱት ድርጅቶች መካከልም “የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል” (CARD) እና “ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች ኢትዮጵያ” (AHRE) ይገኙበታል። ባለሥልጣኑ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ እና በዚህ ሳምንት ለድርጅቶቹ በተናጠል በላከው ደብዳቤ፣ ድርጅቶቹ ከማንኛውም እንቅስቃሴ መታገዳቸውን አስታውቋል ሲል ዋዜማ ሬዲዮ ዘግቧል። ለእገዳው የሰጠው ምክንያት “ከፖለቲካ ገለልተኛ ሆኖ መሥራት ሲገባው ከዓላማው ውጭ በመንቀሳቀስ የአገርና የህዝብ ጥቅምን የሚጎዱ ተግባራት ላይ በመሰማራቱ ከባድ የህግ ጥሰት መፈጸሙን ማረጋገጥ ተችሏል” የሚል ነው። ከሁለቱ የሰብዓዊ ድርጅቶች በተጨማሪ ሌሎችም እንደታገዱ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡ ይህ እርምጃ መንግሥት በሰብአዊ መብት ጉዳዮች ላይ በሚሠሩ ድርጅቶች ላይ ሲያደረግ የቆየው ጫና የመጨረሻ ከፍታ ነው ሲሉ…
Read More
ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ተፋናቃዮችን ደህንነት ማስጠበቅ የሚያስችል ህግ እንደሌላት ተገለጸ

ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ተፋናቃዮችን ደህንነት ማስጠበቅ የሚያስችል ህግ እንደሌላት ተገለጸ

የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በሚገኙባቸው መጠለያዎች ታጣቂዎች ሰርገው እየገቡ ጥቃት መፈጸማቸው ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ዙሪያ ለአንድ ዓመት ያደረገውን ሪፖርት ፋ አድርጓል፡፡ ተቋሙ ከሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. እስከ ሰኔ ወር 2016 ዓ.ም. ድረስ ያለውን ጊዜ የሚሸፍን ሦስተኛውን የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ባለ 52 ገጽ ሪፖርት  ይፋ አድርጓል፡፡ ይህ ሪፖርት የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታን በተመለከተ የለያቸውን መልካም ጅማሮዎች፣ አሳሳቢ ሁኔታዎችን እና ምክረ ሐሳቦችን አካቷል። ኢሰመኮ በአማራ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በጋምቤላ፣ በሐረሪ፣ በኦሮሚያ፣ በሶማሊ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ እና በትግራይ ክልሎች በግጭት እና በተፈጥሮ አደጋ መንስኤዎች የተፈናቀሉ ከ333 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን፣ ተመላሾችን እና ወደ ሌላ ቦታ እንዲሰፍሩ የተደረጉ ተፈናቃዮችን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል እና…
Read More
በአማራ ክልል ከተሞች ሰዎች በዘመቻ እየታሰሩ መሆኑ ተገለጸ

በአማራ ክልል ከተሞች ሰዎች በዘመቻ እየታሰሩ መሆኑ ተገለጸ

ዋና መቀመጫውን አሜሪካ ያደረገው አምንስቲ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ በተለይም በአማራ ክልል ዋና ዋና ከተሞች አዲስ እስር እየተካሄደ እንደሆነ አስታውቋል፡፡ ከመስከረም 18 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የመንገስት የጸጥታ ሀይሎች ዜጎችን ከህግ ውጪ እየያዙ እያሰሩ መሆኑንም ተቋሙ በሪፖርቱ ለይ ጠቅሷል፡፡ በአምንስቲ ኢንተርናሽናል የምስራቅ እና ደቡባዊ አፍሪካ ዳይሬክተር ትግሬ ቻጉታህ እንዳሉት “የኢትዮጵያ የጸጥታ ሀይሎች ንጹሃንን ከህግ ውጪ በዘመቻ ማሰር መጀመራቸው መንግስት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ፍላጎት እንደሌለው ማሳያ ነው” ብለዋል፡፡ ተቋሙ የአይን እማኞችን ጠቅሶ ባወጣው በዚህ ሪፖርቱ ላይ እንደገለጸው ለእስር የተዳረጉ ንጹሃን ህጉ በሚፈቅደው መሰረት በ48 ሰዓት ውስጥ ወደ ፍርድ ቤት እየቀረቡ አለመሆኑንም አስታውቋል፡፡ መንግስት ጀመረው በተባለው የዘመቻ እስር በክልሉ ባሉ ከተሞች የሚገኙ መምህራን እና…
Read More
በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች የዜጎች እገታ መባባሱን ኢሰመኮ ገለጸ

በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች የዜጎች እገታ መባባሱን ኢሰመኮ ገለጸ

በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች በተራዘሙ ግጭቶች ምክንያት የሚፈጸሙ እገታዎች ተባብሰው መቀጠላቸውን  የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል። በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ከተራዘሙ የትጥቅ ግጭቶች ጋር ተያይዞ በአንዳንድ አካባቢዎች በተፈጠረው የሕግ ማስከበር እና የመንግሥት መዋቅር መላላት ሳቢያ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚፈጸሙ እገታዎች መባባሳቸውን ብሏል ኢሰመኮ፡፡ ኢሰመኮ አደረኩት ባለው ማጣራት ለዘረፋ "በተደራጁ ቡድኖች እንዲሁም በአንዳንድ የመንግሥት የጸጥታ አካላት አባሎች" እገታዎች እንደሚፈጸሙ ደርሸበታለሁ ብሏል፡፡  አጋቾች ሰላማዊ ሰዎችን በአብዛኛው በጉዞ (ትራንስፖርት) ላይ እያሉ አንዳንዴም ከመኖሪያ ቤታቸው ወይም ከሥራ ቦታቸው አግተው ወዳልታወቀ ቦታ በመውሰድ ከፍተኛ የማስለቀቂያ ገንዘብ ክፍያ እንደሚጠይቁ ፤ ገንዘብ መክፈል ያልቻሉ በርካታ ታጋቾች ግድያን ጨምሮ በርካታ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች እየተፈጸሙ እንደሚገኙ በሪፖርቱ…
Read More
አሜሪካ በአማራ እና ኦሮሚያ ተማሪዎችን እና ንጹሃን ዜጎችን ማገት እንዲቆም ጠየቀች

አሜሪካ በአማራ እና ኦሮሚያ ተማሪዎችን እና ንጹሃን ዜጎችን ማገት እንዲቆም ጠየቀች

ባሳለፍነው ሳምንት ከደባርቅ ዩንቨርሲቲ ተነስተው ወደ ቤተሰቦቻቸው በመጓዝ ላይ የነበሩ ተማሪዎች መታገታቸው ይታወሳል፡፡ እገታው የተፈጸመው ለአዲስ አበባ ከተማ ትንሽ ሲቀራቸው በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ገብረ ጉራቻ ከተማ አቅራቢያ በታጣቂዎች እንደሆነ በወቅቱ ተገልጾም ነበር፡፡ የፌደራል መንግስትም ሆነ የኦሮሚያ ክልል መንግስት እስካሁን ስለ ጉዳዩ በይፋ እስካሁን ያሉት ነገር ባይኖርም የታጋች ተማሪዎች ቤተሰቦች ግን ልጆቻቸው በታጣቂዎች እንደታገቱባቸው ለተለያዩ ብዙሃን መገናኛዎች ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኢምባሲ በጉዳዩ ዙሪያ በወጣው መግለጫ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች የተራዘሙ ግጭቶች የህግ የበላይነት እንዳይከበር ምክንያት ሆነዋል ሲል በማህበራዊ ትስስር ገጾቹ ላይ ገልጿል፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት እና ከዚህ በፊት የተፈጸሙ ተከታታይ እገታዎች ወንጀለኞችን እንዳይጠየቁ ማድረጉን በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር አረቪን ማሲንጋ መናገራቸውን…
Read More
የጸጥታ ሀይሎች የአማራ ክልል ህዝብ የጤና አገልግሎት እንዳያገኝ እያደረጉ ነው -ሂዩማን ራይትስ ዋች

የጸጥታ ሀይሎች የአማራ ክልል ህዝብ የጤና አገልግሎት እንዳያገኝ እያደረጉ ነው -ሂዩማን ራይትስ ዋች

የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ አጋሮች በአማራ ክልል እየተፈጸመ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳላየ መሆናቸውን እንዲያቆሙ ሂዩማን ራይትስ ዋች አሳሰበ፡፡ ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተቋም ሂዩማን ራይትስ ዋች በኢትዮጵያ አማራ ክልል የሰብዓዊ መብት ጥሰት ዙሪያ አዲስ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ የተቋሙ ሪፖርት ካሳለፍነው ነሀሴ 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 2016 ዓ.ም ባሉት 10 ወራት ውስጥ ተፈጽመዋል ባለቸው ጉዳዮች ዙሪያ አተኩሯል፡፡ በአማራ ክልል ከጤና እና ተያያዥ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ዙሪያ ያተኮረው ይህ ሪፖርት የመንግስት የጸጥታ ሀይሎች የጤና ተቋማትን ኢላማ አድርገዋል ብሏል፡፡ ተቋሙ 58 ተጎጂዎችን እና የአይን ምስክሮችን ቃለ መጠይቅ አድርጌ አወጣሁት ባለው ሪፖርቱ ላይ እንዳለው ወታደሮች ለህክምና ወደ ሆስፒታል ሲገቡ ቢሞቱ ሐኪሞቹ ተጠያቂ እንደሚሆኑ…
Read More
ብሪታንያ በኢትዮጵያ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ለማቅረብ የ125 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አደረገች

ብሪታንያ በኢትዮጵያ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ለማቅረብ የ125 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አደረገች

የብሪታንያ የአፍሪካ ልማት ዳይሬክተር በኢትዮጵያ ለሁለት ቀናት ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን ከጉብኝቱ በኋላ ድጋፉን አድርገዋል ተብሏል። ሚንስትሩ ከጉብኝታቸው በኋላ እንዳሉት አሳሳቢ የምግብ ዋስትና ችግር ያለባቸው ኢትዮጵያውያን ቁጥር በቀጣይ ወራት 10 ነጥብ 8 ሚሊየን ይደርሳክ ብለዋል። የ125 ሚሊየን ዶላር ድጋፉ ለሶስት ሚሊየን ሰዎች ህይወት አድን እርዳታ ለማቅረብ እንደሚውልም ተገልጿል። አስቸኳይ ድጋፉ በአልሚ ምግብና ሌሎች ወሳኝ ግብአቶች ምክንያት እየተከሰተ የሚገኘውን ሞት ለመቀነስ ለ75 የጤና ተቋማት የተለያዩ ድጋፎችን ለማቅረብ ነውም ተብሏል። የአውሮፓ ህብረት ከአንድ ወር በፊት በኢትዮጵያ በድርቅ እና ግጭቶች ለተፈናቀሉ ዜጎች 2 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉ ይታወሳል። በኢትዮጵያ በጦርነት እና ድርቅ ምክንያቶች ለእርዳታ የሚዳረጉ ዜጎች ቁጥር እየጨመረ የመጣ በመምጣት ላይ ይገኛል።…
Read More
በኦሮሚያ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ 11 ሰዎች ተገደሉ

በኦሮሚያ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ 11 ሰዎች ተገደሉ

በአማራ፣ ኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መቀጠላቸውን ኢሰመኮ ገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ፣ኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ዙሪያ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ እንደ ኢሰመኮ ሪፖርት ከሆነ በአማራ ክልል በአዊ ብሔረሰብ ዞን፣ በአየሁ ጓጉሳ ወረዳ እና በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ቡሬ ዙሪያ ወረዳ፤ እንዲሁም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ አሶሳ ዞን፣ ኦዳ ብልድግሉ ወረዳ፤ በተጨማሪም በኦሮሚያ ክልል፣ በአርሲ ዞን፣ ሸርካ ወረዳ እና በቄለም ወለጋ ዞን፣ ጊዳሚ ወረዳ በሲቪል ሰዎች ላይ ጥቃቶች መፈጸማቸውን ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡ በአማራ ክልል፣ በአዊ ብሔረሰብ ዞን አስተዳደር፣ በአየሁ ጓጉሳ ወረዳ፣ አምበላ ቀበሌ እና በዚገም ወረዳ ሶሪት ቀበሌ ከጥቅምት 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ…
Read More