Passportservice

በኢትዮጵያ ፓስፖርት ቤት ለቤት ማደል ሊጀመር ነው ተባለ

በኢትዮጵያ ፓስፖርት ቤት ለቤት ማደል ሊጀመር ነው ተባለ

በኢትዮጵያ ባለፉት 12 ወራት ውስጥ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ለሆኑ ሰዎች ፓስፖርት ተሰጥቷል ተብሏል የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዓመታዊ አፈጻጸሙን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት እንዳሉት በ2016 አመት 1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ፓስፖርት ለአመልካቾ መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ በታሪኩ ይህን መጠን ያለዉ ፓስፖርት ለአገልግሎት ፈላጊዎች ሲሰጥ የመጀመሪያዉ መሆኑን ዳይሬክተሯ ጠቅሰዋል። ይህ በዚህ እንዳለም ተቋሙ ከፓስፖርት እና ሌሎች አገልግሎት ክፍያዎች 14 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱንም ተናግረዋል። የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ጭምር ቅሬታ ሲቀርብበት ቢሰማም እንዲሁም ተገልጋዮች አሁንም ቅሬታ ማቅረባቸዉን ቢቀጥሉም ፤ ተቋሙ አሰራሮቼን እያስተካከልኩ እገኛለሁ ብሏል። ዋና ዳይሬክተሯ ፤ ከዚህ…
Read More