Passport

ከ3 ሺህ በላይ ሰዎች ፓስፖርት በህገወጥ መልኩ ለማግኘት ሲሞክሩ መታሰራቸው ተገለጸ

ከ3 ሺህ በላይ ሰዎች ፓስፖርት በህገወጥ መልኩ ለማግኘት ሲሞክሩ መታሰራቸው ተገለጸ

ባለፋት ዘጠኝ ወራት በህገ ወጥ መንገድ የፓስፓርት አግልግሎት ለማግኘት የሞከሩ ከ3 ሺህ በላይ ሰዎች በቁጥጥር ስር ዉለዋል ተብሏል። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በ2018 በጀት አመት ዘጠኝ ወራት ያከናወናቸውን አገልግሎት አፈፃፀም በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት እንደተናገሩት ባለፋት ዘጠኝ ወራት 3 ሺህ 6 መቶ 38 ግለሰቦች በህገ ወጥ መንገድ የፓስፓርት አግልግሎት ለማግኘት የተጭበረበረ ሰነድ ይዘው ሲንቀሳቀሱ ነበር። ከፓስፖርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ  300 የውጭ ዜጎች እና 3ሺህ3 መቶ 38 ኢትዮጵያውያን በህገ ወጥ መንገድ አገልግሎት ለማግኘት የተጭበረበረ ሰነድ ይዞው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ እና ትክክለኛ ያልሆነ የዜግነት ማስረጃ ይዘዉ የተገኙ መሆናቸው ተጠቁሟል። በዚህም መሰረት በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጋቸውን…
Read More
በአንድ ዓመት ውስጥ ከ1.4 ሚሊዮን በላይ ፓስፖርት መሰጠቱ ተገለጸ

በአንድ ዓመት ውስጥ ከ1.4 ሚሊዮን በላይ ፓስፖርት መሰጠቱ ተገለጸ

የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በ2017 በጀት ዓመት ለ1.4 ሚሊዮን ዜጎች ፓስፖርት መስጠቱን አስታውቋል። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት እንዳሉት ለፓስፖርት አመልካቾች የተቀላጠፈ አገልግሎት በመሰጠቱ ምክንያት የአመልካቾች ቁጥር ቀንሷል ብለዋል። ተቋሙ የኢ-ፓስፖርት ለመስጠት ያስቀመጠውን እቅድ በአዲስ አበባ ጎተራ ባለው ቅርንጫፍ ማስጀመሩም ተገልጿል። ይሁንና ተቋሙ ፓስፖርት ቤት ለቤት መስጠት እጀምራለሁ በሚል የያዘው እቅድ እስካሁን ስለመጀመሩ ዳይሬክተሯ አልገለጹም። ይህ በዚህ እንዳለም የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ከ3800 በላይ ሰዎች በተጭበረበረ ሰነድ ፓስፖርት ለማውጣት ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር ውለዋል ተብሏል። ተቋሙ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ፓስፖርት ለማግኘት የሚሞክሩ ሰዎችን የመቆጣጠሩ አቅሙ ያደገው ተቋማዊ ደህንነትን የማረጋጫ ሥርዓት ዘርግቷልም ተብሏል።  ከፓስፖርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ከሰራተኞች ጋር በመመሳጠር ተገልጋዮችን በማጉላላት እና…
Read More
ኢትዮጵያ ለ10 ዓመት የሚያገለግል አዲስ ፓስፖርት ይፋ አደረገች

ኢትዮጵያ ለ10 ዓመት የሚያገለግል አዲስ ፓስፖርት ይፋ አደረገች

ኢትዮጵያ አራት አይነት ፓስፖርቶችን በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጋለች የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አዲስ ፓስፖርቶችን ይፋ አድርጓል። ዛሬ በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም ይፋ የተደረጉት ፓስፖርቶች አራት አይነት ሲሆኑ ከመደበኛ ፓስፖርት በተጨማሪ የዲፕሎማት፣ ውጭ ሀገራት እና የአገልግሎት ፓስፖርቶችም ይገኙበታል። ፓስፖርቶቹ በጃፓኑ ቶፓን የደህንነት ኩባንያ እና በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ኩባንያ ትብብር ስለመመረቱም ተገልጿል። 10 ዓመት እንዲያገለግል ተደርጎ የተሰራው ይህ ፓስፖርት በአዲስ አበባ በሚገኘው ቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የተመረተ ነው። የፓስፖርቱ አገልግሎት ጊዜ 10 ዓመት መደረግ የዜጎችን ጊዜ፣ ገንዘብ እና ጉልበት እንደሚቆጥብ ተገልጿል። ይህ በዚህ እንዳለም በፓስፖርቱ ውስጥ ገጾች ላይ የኢትዮጵያን መልካም ገጽታዎች የሚያጎለብቱ እና ታሪካዊ ቅርጾችን ይዟልም ተብሏል። እንዲሁም ፓስፖርቱ የማይክሮ ችፕስ የተገጠመለት…
Read More
ከፓስፖርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ሙስና ፈጽመዋል የተባሉ 42 ተጠርጣሪዎች ታሰሩ

ከፓስፖርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ሙስና ፈጽመዋል የተባሉ 42 ተጠርጣሪዎች ታሰሩ

የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሰራተኞች ህዝብን ከማማረራቸው ባለፈ ለውጭ ሀገራት ዜጎች ፓስፖርት ሲሰጡ ነበርም ተብሏል፡፡ በሙስና ተጠርጥረው በፖሊስ ከታሰሩ ሰዎች መካከል የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተሩ ይገኙበታል፡፡ 42 የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሰራተኞች ባሳለፍነው ሰኞ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በህግ ቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ የመንግሥት አስተዳደር ለውጥ ከተደረገ ጀምሮ የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ተቋም ውስጥ የተለያዩ ለውጦች (ሪፎርም) የተደረገ ቢሆንም፣ አንዳንድ የተቋሙ ሠራተኞች በድለላ ሥራ የተሰማሩ አካላት ጋር በመመሳጠር የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል ተብለው በቁጥጥር ሥር ውለው በምርመራ ላይ ናቸው ተብሏል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ባሳለፍነው ሀምሌ ወር ላይ ፓስፖርት ፈላጊ ኢትዮጵያዊያን መንገላታታቸውን ተከትሎ የተቋሙን አመራሮች ከስልጣን አግደው ነበር፡፡ ሰላማዊት ዳዊት ደግሞ…
Read More
ኢትዮጵያ የመዳረሻ ቪዛን ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ መስጠት እንደምትጀምር ገለጸች

ኢትዮጵያ የመዳረሻ ቪዛን ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ መስጠት እንደምትጀምር ገለጸች

ኢትዮጵያ የመዳረሻ ቪዛ አገልግሎት ለውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ከሁለት ዓመት በፊት መስጠት የጀመረች ቢሆንም በኮሮና ቫይረስ እና በሌሎች ምክንያቶች ተቋርጦ ቆይቷል፡፡ የጎብኚዎችን ቁጥር ከፍ እንደሚያደርግ የሚገለጸው የመዳረሻ ቮዛ አገልግሎት ከመስከረም 15 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ኢትዮጵያ 190 ሺህ ፓስፖርት ከውጪ ሀገር በማሳተም ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባቷን ገልጻለች፡፡ የኢምግሬሽን እና ዝግጅት አገልግሎት ከሙስና ጋር በተያያዘ ሁሉንም ከፍተኛ አመራሮች ከሀላፊነት በማንሳት አዲስ አመራር ከአንድ ወር በፊት ተሾሞለታል። ባሳለፍነው ሀምሌ ወር ላይ ተቋሙን በሀላፊነት እንዲመሩ በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ (ዶ/ር) የተሾሙት ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት በጉዳዩ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሯ በመግለጫቸው 300 ሺህ ዜጎች ፓስፖርት ለማግኘት ተመዝግበው እየተጠባበቁ መሆኑን…
Read More
ሰላምዊት ዳዊት የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሀላፊ ሆነው ተሾሙ

ሰላምዊት ዳዊት የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሀላፊ ሆነው ተሾሙ

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ሰላማዊት ዳዊትን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ሀላፊ አድርገው ሾሙ። የኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት ሶስት ከፍተኛ አመራሮች ከሀላፊነት መነሳታቸው ተገልጿል። ፓስፖርት እና መሰል የዜግነት አገልግሎቶችን ለመስጠት የተቋቋመው የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ተቋም ቅሬታዎች ሲቀርቡበት ቆይተዋል። ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ላለፉት አንድ ዓመት ከመንፈቅ የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎትን በዋና ዳይሬክተርነት ሲመሩ የነበሩት አቶ ብሩህተስፋ ሙልጌታን፣ በምክትል ዳይሬክተርነት ሲያገለግሉ የነበሩት ፍራኦል ጣፋ እና ታምሩ ግንበቶን ከኅላፊነት አንስተዋል። የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ህዝብ ግንኙነት እና ኮሙንኬሽን ሀላፊ ወይዘሮ ማስታዋል ገዳ ለአልዓይን እንዳሉት ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት ከሰኔ 12 ቀን 2015 ዓም ጀምሮ ተቋሙን በዋና ዳይሬክተርነት እንዲመሩ መሾማቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ደርሶናል ብለዋል። እንዲሁም…
Read More