Visaonarrival

ኢትዮጵያ ከ14 ሺህ በላይ የውጭ ሀገራት ዜጎች የመኖሪያ ፈቃድ ሰጠች

ኢትዮጵያ ከ14 ሺህ በላይ የውጭ ሀገራት ዜጎች የመኖሪያ ፈቃድ ሰጠች

ሀገሪቱ ለ20 የውጭ ዜግነት ለነበራቸው ሰዎች የኢትዮጵየዊ ዜግነት ሰጥታለች ተብሏል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት የተቋሙን የስድስት ወራት አፈጻጸም አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ዳይሬክተሯ በመግለጫቸው ላይ እንዳሉት ለ14 ሺህ 367 ለሚሆኑ የውጭ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የመኖሪያ ፍቃድ ተሰጥቷቸዋል ብለዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ለ20 ግለሰቦች ደግሞ የኢትዮጵያዊ ዜግነት እንደተሰጣቸውም ወይዘሮ ሰላማዊት በመግለጫው ለይ ጠቅሰዋል። ተቋሙ ለዜጎች የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት የሠው ሀይሉን የማጠናከር፤ አሰራሩን በቴክኖሎጂ የማገዝ ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል። በኢትዮጵያ ለጉብኝት ቱሪስት፣ ለኮንፍረንስና ለቢዝነስ የሚገቡትን ለማስተናገድ በ188 ሀገራት ቪዛ ኦን አራይቫል በመክፈት እየተሰራ መሆኑም ዳይሬክተሯ ተናግረዋል፡፡ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከ1 ነጥብ 6 ሚሊየን ሚሊዮን በላይ ሰዎች በአየር ትራንስፖርት ወደ ኢትዮጵያ…
Read More
ኢትዮጵያ የመዳረሻ ቪዛን ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ መስጠት እንደምትጀምር ገለጸች

ኢትዮጵያ የመዳረሻ ቪዛን ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ መስጠት እንደምትጀምር ገለጸች

ኢትዮጵያ የመዳረሻ ቪዛ አገልግሎት ለውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ከሁለት ዓመት በፊት መስጠት የጀመረች ቢሆንም በኮሮና ቫይረስ እና በሌሎች ምክንያቶች ተቋርጦ ቆይቷል፡፡ የጎብኚዎችን ቁጥር ከፍ እንደሚያደርግ የሚገለጸው የመዳረሻ ቮዛ አገልግሎት ከመስከረም 15 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ኢትዮጵያ 190 ሺህ ፓስፖርት ከውጪ ሀገር በማሳተም ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባቷን ገልጻለች፡፡ የኢምግሬሽን እና ዝግጅት አገልግሎት ከሙስና ጋር በተያያዘ ሁሉንም ከፍተኛ አመራሮች ከሀላፊነት በማንሳት አዲስ አመራር ከአንድ ወር በፊት ተሾሞለታል። ባሳለፍነው ሀምሌ ወር ላይ ተቋሙን በሀላፊነት እንዲመሩ በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ (ዶ/ር) የተሾሙት ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት በጉዳዩ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሯ በመግለጫቸው 300 ሺህ ዜጎች ፓስፖርት ለማግኘት ተመዝግበው እየተጠባበቁ መሆኑን…
Read More