Visaonarrival

ከ3 ሺህ በላይ ሰዎች ፓስፖርት በህገወጥ መልኩ ለማግኘት ሲሞክሩ መታሰራቸው ተገለጸ

ከ3 ሺህ በላይ ሰዎች ፓስፖርት በህገወጥ መልኩ ለማግኘት ሲሞክሩ መታሰራቸው ተገለጸ

ባለፋት ዘጠኝ ወራት በህገ ወጥ መንገድ የፓስፓርት አግልግሎት ለማግኘት የሞከሩ ከ3 ሺህ በላይ ሰዎች በቁጥጥር ስር ዉለዋል ተብሏል። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በ2018 በጀት አመት ዘጠኝ ወራት ያከናወናቸውን አገልግሎት አፈፃፀም በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት እንደተናገሩት ባለፋት ዘጠኝ ወራት 3 ሺህ 6 መቶ 38 ግለሰቦች በህገ ወጥ መንገድ የፓስፓርት አግልግሎት ለማግኘት የተጭበረበረ ሰነድ ይዘው ሲንቀሳቀሱ ነበር። ከፓስፖርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ  300 የውጭ ዜጎች እና 3ሺህ3 መቶ 38 ኢትዮጵያውያን በህገ ወጥ መንገድ አገልግሎት ለማግኘት የተጭበረበረ ሰነድ ይዞው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ እና ትክክለኛ ያልሆነ የዜግነት ማስረጃ ይዘዉ የተገኙ መሆናቸው ተጠቁሟል። በዚህም መሰረት በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጋቸውን…
Read More
ኢትዮጵያ ከ14 ሺህ በላይ ለውጭ ሀገራት ዜጎች የመኖሪያ ፈቃድ ሰጠች

ኢትዮጵያ ከ14 ሺህ በላይ ለውጭ ሀገራት ዜጎች የመኖሪያ ፈቃድ ሰጠች

ሀገሪቱ ለ20 የውጭ ዜግነት ለነበራቸው ሰዎች የኢትዮጵየዊ ዜግነት ሰጥታለች ተብሏል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት የተቋሙን የስድስት ወራት አፈጻጸም አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ዳይሬክተሯ በመግለጫቸው ላይ እንዳሉት ለ14 ሺህ 367 ለሚሆኑ የውጭ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የመኖሪያ ፍቃድ ተሰጥቷቸዋል ብለዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ለ20 ግለሰቦች ደግሞ የኢትዮጵያዊ ዜግነት እንደተሰጣቸውም ወይዘሮ ሰላማዊት በመግለጫው ለይ ጠቅሰዋል። ተቋሙ ለዜጎች የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት የሠው ሀይሉን የማጠናከር፤ አሰራሩን በቴክኖሎጂ የማገዝ ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል። በኢትዮጵያ ለጉብኝት ቱሪስት፣ ለኮንፍረንስና ለቢዝነስ የሚገቡትን ለማስተናገድ በ188 ሀገራት ቪዛ ኦን አራይቫል በመክፈት እየተሰራ መሆኑም ዳይሬክተሯ ተናግረዋል፡፡ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከ1 ነጥብ 6 ሚሊየን ሚሊዮን በላይ ሰዎች በአየር ትራንስፖርት ወደ ኢትዮጵያ…
Read More
ኢትዮጵያ የመዳረሻ ቪዛን ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ መስጠት እንደምትጀምር ገለጸች

ኢትዮጵያ የመዳረሻ ቪዛን ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ መስጠት እንደምትጀምር ገለጸች

ኢትዮጵያ የመዳረሻ ቪዛ አገልግሎት ለውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ከሁለት ዓመት በፊት መስጠት የጀመረች ቢሆንም በኮሮና ቫይረስ እና በሌሎች ምክንያቶች ተቋርጦ ቆይቷል፡፡ የጎብኚዎችን ቁጥር ከፍ እንደሚያደርግ የሚገለጸው የመዳረሻ ቮዛ አገልግሎት ከመስከረም 15 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ኢትዮጵያ 190 ሺህ ፓስፖርት ከውጪ ሀገር በማሳተም ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባቷን ገልጻለች፡፡ የኢምግሬሽን እና ዝግጅት አገልግሎት ከሙስና ጋር በተያያዘ ሁሉንም ከፍተኛ አመራሮች ከሀላፊነት በማንሳት አዲስ አመራር ከአንድ ወር በፊት ተሾሞለታል። ባሳለፍነው ሀምሌ ወር ላይ ተቋሙን በሀላፊነት እንዲመሩ በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ (ዶ/ር) የተሾሙት ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት በጉዳዩ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሯ በመግለጫቸው 300 ሺህ ዜጎች ፓስፖርት ለማግኘት ተመዝግበው እየተጠባበቁ መሆኑን…
Read More