Selamawitdawit

ሰላምዊት ዳዊት የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሀላፊ ሆነው ተሾሙ

ሰላምዊት ዳዊት የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሀላፊ ሆነው ተሾሙ

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ሰላማዊት ዳዊትን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ሀላፊ አድርገው ሾሙ። የኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት ሶስት ከፍተኛ አመራሮች ከሀላፊነት መነሳታቸው ተገልጿል። ፓስፖርት እና መሰል የዜግነት አገልግሎቶችን ለመስጠት የተቋቋመው የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ተቋም ቅሬታዎች ሲቀርቡበት ቆይተዋል። ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ላለፉት አንድ ዓመት ከመንፈቅ የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎትን በዋና ዳይሬክተርነት ሲመሩ የነበሩት አቶ ብሩህተስፋ ሙልጌታን፣ በምክትል ዳይሬክተርነት ሲያገለግሉ የነበሩት ፍራኦል ጣፋ እና ታምሩ ግንበቶን ከኅላፊነት አንስተዋል። የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ህዝብ ግንኙነት እና ኮሙንኬሽን ሀላፊ ወይዘሮ ማስታዋል ገዳ ለአልዓይን እንዳሉት ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት ከሰኔ 12 ቀን 2015 ዓም ጀምሮ ተቋሙን በዋና ዳይሬክተርነት እንዲመሩ መሾማቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ደርሶናል ብለዋል። እንዲሁም…
Read More