Korea

ኤልጂ ለቃኝው ሻለቃ ዘማች ቤተሰቦች የሙዚቃ ስቱዲዮ ሊገነባ ነው

ኤልጂ ለቃኝው ሻለቃ ዘማች ቤተሰቦች የሙዚቃ ስቱዲዮ ሊገነባ ነው

​የደቡብ ኮሪያው የኤሌክትሮኒክስ ግዙፍ ኩባንያ ኤልጂ (LG)፣ በኮሪያ ጦርነት ወቅት ለተሳተፉት የኢትዮጵያ ቃኝው ሻለቃ ዘማቾች የልጅ ልጆች ለተዋቀረው "ቃኝው ክዋየር"  ዘመናዊ የልምምድ ስቱዲዮ ሊገነባ መሆኑን አስታውቋል። ​ስቱዲዮው በአዲስ አበባ በሚገኘው የኮሪያ አርበኞች መታሰቢያ ህንፃ ውስጥ የሚገነባ ሲሆን፣ የድምፅ መከላከያ ፣ ዘመናዊ የድምፅ ሲስተም እና ዲጂታል የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች እንደሚሟሉለት ተገልጿል። ኤልጂ ይህንን የበጎ አድራጎት ፕሮጀክት የሚያከናውነው ከኮሪያ የሀገር ፍቅርና የአርበኞች ጉዳይ ሚኒስቴር እና "Warm Mind" ከተባለው መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር ነው። ​በ2018 የተቋቋመው ይህ የሙዚቃ ቡድን፣ እስካሁን ድረስ ቋሚ የልምምድ ቦታ ባለመኖሩ እና የቴክኖሎጂ ቁሳቁስ እጥረት በነበረበት ሁኔታ የባህል አምባሳደር በመሆን የኢትዮጵያ ባህላዊ ሙዚቃዎችን እና እንደ "አሪራንግ" ያሉ የኮሪያ ታዋቂ…
Read More
አዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ 150 ሺህ ዶላር የሚያወጡ ድጅታል ብሬሎችን ተረከበ

አዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ 150 ሺህ ዶላር የሚያወጡ ድጅታል ብሬሎችን ተረከበ

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እያንዳንዳቸው አምስት ሺህ ዶላር የሚያወጡ 30 ዘመናዊ ዲጂታል ብሬሎችን መረከቡን ገልጿል። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከደቡብ ኮሪያው ሴሎም ኢንተርናሽናል ኮኦፕሬሽን ኤጀንሲ ጋር በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመው ነበር፡፡ በዚህ ስምምነት መሰረትም እያንዳንዳቸው አምስት ሺህ ዶላር የሚያወጡ 30 ዲጂታል ብሬሎችን እንደተረከበ አስታውቋል፡፡ ዩንቨርሲቲው እንዳስታወቀው በቀጣይ ደግሞ ተመሳሳይ ቀሪ 30 ብሬሎችን በድጋፍ እንደሚረከብ ገልጿል። ይህ ዘመናዊ መሳሪያ ማየት የተሳናቸው  የዩኒቨርሲቲያችን የቅድመ እና ድህረ-ምረቃ ተማሪዎች ከወረቀት ብሬል ተላቀው በቴክኖሎጂ በመታገዝ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ የሚረዳ ሲሆን፤ ከተለያዩ ዳታቤዞችም ጥናታዊ ጽሑፎችን ያለምንም ክፍያ አውረደው መጠቀም ያስችላቸዋል ተብሏል። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአምስት አመት ስትራቴጂክ እቅዱ መሰረት ለዲጂታላይዜሽን ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡ አዲስ አበባ…
Read More
ደቡብ ኮሪያ በኢትዮጵያ ግብርናን ለማዘመን 10 ሚሊዮን ዶላር ለገሰች

ደቡብ ኮሪያ በኢትዮጵያ ግብርናን ለማዘመን 10 ሚሊዮን ዶላር ለገሰች

ኢትዮጵያ እና የኮሪያ ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ የ10 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ስምምነትን በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል። የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የኮይካ ሃላፊ ሊ ቢዩንግህዋ ፈርመውታል። የገንዘብ ድጋፉ የኢትዮጵያን ግብርና ለማዘመን ይውላል የተባለ ሲሆን በተለይም የወተት እና የወተት ተዋጽኦ ምርታማነትን ለማሳደግ ያስችላል ተብሏል። የወተት ምርታማነትን የሚያሳድገው ይህ ፕሮጀክት በቀጣዮቹ ስድስት ዓመታት እንደሚተገበር የገንዘብ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ፕሮጄክቱ በወተት ልማት እና እንስሳት እርባታ ዘርፍ የተሰማሩ አርሶ አደሮችን መደገፍ ላይ ትኩረቱን እንደሚያደርግም ተገልጿል። የተሻሻሉ የወተት ላሞችን ለአርሶ አደሩ ማቅረብ፣ የወተት ምርታማነትን መጨመር፣ በማህበር የተደራጁ ወተት አቅራቢዎችን የገበያ እድሎችን ማስፋት፣ ተጨማሪ ሌሎች አሰራሮችን መዘርጋት የፕሮጀክቱ ዓላማ ነው ተብሏል።…
Read More