Milkproduction

ደቡብ ኮሪያ በኢትዮጵያ ግብርናን ለማዘመን 10 ሚሊዮን ዶላር ለገሰች

ደቡብ ኮሪያ በኢትዮጵያ ግብርናን ለማዘመን 10 ሚሊዮን ዶላር ለገሰች

ኢትዮጵያ እና የኮሪያ ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ የ10 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ስምምነትን በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል። የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የኮይካ ሃላፊ ሊ ቢዩንግህዋ ፈርመውታል። የገንዘብ ድጋፉ የኢትዮጵያን ግብርና ለማዘመን ይውላል የተባለ ሲሆን በተለይም የወተት እና የወተት ተዋጽኦ ምርታማነትን ለማሳደግ ያስችላል ተብሏል። የወተት ምርታማነትን የሚያሳድገው ይህ ፕሮጀክት በቀጣዮቹ ስድስት ዓመታት እንደሚተገበር የገንዘብ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ፕሮጄክቱ በወተት ልማት እና እንስሳት እርባታ ዘርፍ የተሰማሩ አርሶ አደሮችን መደገፍ ላይ ትኩረቱን እንደሚያደርግም ተገልጿል። የተሻሻሉ የወተት ላሞችን ለአርሶ አደሩ ማቅረብ፣ የወተት ምርታማነትን መጨመር፣ በማህበር የተደራጁ ወተት አቅራቢዎችን የገበያ እድሎችን ማስፋት፣ ተጨማሪ ሌሎች አሰራሮችን መዘርጋት የፕሮጀክቱ ዓላማ ነው ተብሏል።…
Read More