SouthKorea

ደቡብ ኮሪያ ለኢትዮጵያ የ10 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አደረገች

ደቡብ ኮሪያ ለኢትዮጵያ የ10 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አደረገች

በኢትዮጵያና በኮሪያ ሪፐብሊክ መንግስት መካከል የ10 ሚሊዮን ዶላር የፕሮጀክት ድጋፍ ስምምነት ተፈርሟል፡፡ ስምምነቱ በኢትዮጵያ ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና በኮሪያ ሪፐብሊክ አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ መካከል የኢትዮጵያ የጥራት አመራር አቅም ማጎልበቻ ፐሮጀክት ነው፡፡ ፕሮጀክቱ የግብርና እና የተቀናበሩ የግብርና ምርት ውጤቶች ተወዳዳሪነትን ማሳደግ ላይ ያተኩራል የተባለ ሲሆን ለዚህም ደቡብ ኮሪያ ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ 10 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ታደርጋለች ተብሏል፡፡ በፊርማ ስነስርዓቱ በኢትዮጵያ የኮሪያ አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ ዳይሬክተር ሚስተር ሃን ዲዩግ ቾ እንደገለፁት የኢትዮጵያና የኮሪያ ሪፐብሊክ ግንኙነት ታረካዊ ነው ያሉ ሲሆን በኮሪያ ጦርነት ወቅት ከ6000 በላይ የኢትዮጵያ ወታደሮች ለኮሪያ ህዝብ ተዋግተው የደም ዋጋ የከፈሉ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የፕሮጀክት ስምምነቱ የኮሪያ እና የኢትዮጵያ ወዳጅነትን…
Read More
ደቡብ ኮሪያ በኢትዮጵያ ግብርናን ለማዘመን 10 ሚሊዮን ዶላር ለገሰች

ደቡብ ኮሪያ በኢትዮጵያ ግብርናን ለማዘመን 10 ሚሊዮን ዶላር ለገሰች

ኢትዮጵያ እና የኮሪያ ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ የ10 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ስምምነትን በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል። የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የኮይካ ሃላፊ ሊ ቢዩንግህዋ ፈርመውታል። የገንዘብ ድጋፉ የኢትዮጵያን ግብርና ለማዘመን ይውላል የተባለ ሲሆን በተለይም የወተት እና የወተት ተዋጽኦ ምርታማነትን ለማሳደግ ያስችላል ተብሏል። የወተት ምርታማነትን የሚያሳድገው ይህ ፕሮጀክት በቀጣዮቹ ስድስት ዓመታት እንደሚተገበር የገንዘብ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ፕሮጄክቱ በወተት ልማት እና እንስሳት እርባታ ዘርፍ የተሰማሩ አርሶ አደሮችን መደገፍ ላይ ትኩረቱን እንደሚያደርግም ተገልጿል። የተሻሻሉ የወተት ላሞችን ለአርሶ አደሩ ማቅረብ፣ የወተት ምርታማነትን መጨመር፣ በማህበር የተደራጁ ወተት አቅራቢዎችን የገበያ እድሎችን ማስፋት፣ ተጨማሪ ሌሎች አሰራሮችን መዘርጋት የፕሮጀክቱ ዓላማ ነው ተብሏል።…
Read More