Visaban

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ላይ የጣለውን የቪዛ ገደብ አነሳ

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ላይ የጣለውን የቪዛ ገደብ አነሳ

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የነበረውን የቪዛ ገደብ ከሁለት ዓመት በኋላ አንስቻለሁ ብሏል፡፡ ህብረቱ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ ሚያዝያ 2016 ወደ አውሮፓ በሚጓዙ ኢትዮጵያውያን ቪዛ  አመልካቾች ላይ ገደቦችን ጥሎ እንደነበር ገልጾ ገደቡ መነሳቱን አስታውቋል፡፡ ህብረቱ የቪዛ ገደቦቹን የጣለው በተለያዩ ጊዜያት ወደ ህብረቱ አባል ሀገራት የገቡ እና የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ኢትዮጵያዊያንን የኢትዮጵያ መንግስት ለመመለስ እየተባበረ አይደለም በሚል ምክንያት ነበር፡፡ ከሁለት ወራት በፊት በአዲስ አበባ በተካሄደው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት የሁለትዮሽ ውይይት ላይ በአውሮፓ ሀገራት የመኖሪያ ፈቃድ ያላገኙ ኢትዮጵያዊያንን ወደ ሀገራቸው ከመመለስ አንጻር የኢትዮጵያ መንግስት ያሳየውን መሻሻል አድንቆ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት በኢትዮጵያ ላይ ከጣላቸው የቪዛ ገደቦች መካከልም የቪዛ ማመልከቻ ጊዜ…
Read More