ዜና

ኢትዮጵያና ጅቡቲ ሁለተኛውን የኃይል መስመር ዝርጋታ ስምምነት ተፈራረሙ

ኢትዮጵያና ጅቡቲ ሁለተኛውን የኃይል መስመር ዝርጋታ ስምምነት ተፈራረሙ

የኢትዮጵያን ጋላፊ ማከፋፈያ ጣቢያ ከጅቡቲው ናጋድ ማከፋፈያ ጣቢያ ጋር በሚያገናኘው በዚህ ፕሮጀክት፤ የ230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ እንደሚከናወን በጅቡቲ በተካሄደው የፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ ተገልጿል፡፡ በጅቡቲ ግዛት የሚዘረጋውን 190 ኪሎ ሜትር ጨምሮ በአጠቃላይ 292 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን የኃይል መስመር ፕሮጀክት በ18 ወራት ለማጠናቀቅ እቅድ መያዙ ተዘግቧል፡፡ ዓለም ባንክ ዝርጋታውን በ55 ሚሊዮን ዶላር ብድር የሚደግፈው ሲሆን፤ የግንባታ ውሉ ትራንስሬይል ሊሚትድ ለተሰኘ የህንድ ኢንጂነሪንግ ኩባንያ መሰጠቱን ስፑትኒክ ዘግቧል፡፡ የጅቡቲ የኢነርጂ እና የተፈጥሮ ሀብት ሚኒስትር ዮኒስ አሊ ጉዲ፤ “ፕሮጀክቱ ታዳሽ የኃይል ሀብቶችን በመጠቀም ላይ የተመሠረተ ብሔራዊ የኃይል ፖሊሲ እንድንተገብር ይረዳናል፣ ይህም 100 በመቶ የንጹህ ኃይል ግባችንን እንድናሳካ ያስችለናል” ሲሉ ተናግረዋል። የኃይል መስመር…
Read More
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባሕል ማዕከል እና ዲኤስቲቪ በመተባበር ያዘጋጁት የጥበብ ምሽት ተካሄደ 

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባሕል ማዕከል እና ዲኤስቲቪ በመተባበር ያዘጋጁት የጥበብ ምሽት ተካሄደ 

"የአንድ ግጥም አንድ ወግ" ኪነ ጥበባዊ ዝግጅት በድምቀት የተከናወነ ሲሆን በዲኤስቲቪ አቦል ቴሌቪዥን የሚተላለፉ ተወዳጅ ድራማዎችን እያቀረቡ ያሉት ተዋናዮችና ፕሮዲዩሰሮች የዝግጅቱ ልዩ እንግዶች በመሆን ልምዳቸውን አካፍለዋል።  የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባሕል ማዕከል ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር ተስፋዬ እሸቱ " በሀገራችን የኪነ ጥበብና በተለይም በቴሌቪዥን ተከታታይ ፊልም ስራዎች ጉልህ አበርክቶ እያከናወነ ካለው ዲኤስቲቪ አቦል ቴሌቪዥን ጋር በትብብር የጥበብ መድረክ ማዘጋጀታችን ወደፊትም ይቀጥላል። ከሌሎች ተባባሪ አካላት ጋርም በትብብር ለመስራት ባሕል ማዕከላችን ክፍት ነው" ሲሉ በመክፈቻ ዝግጅቱ ወቅት ተናግረዋል።  የዲኤስቲቪ ኢትዮጵያ የማርኬቲንግ ኃላፊ ወ/ሮ ትህትና ተስፋዬ በበኩላቸው " እኔ እና ዲኤስቲቪ" በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የብራንድ ትውውቅ ከ አአዩ ባሕል ማዕከል ጋር መዘጋጀቱን ገልፀው አብዛኛው…
Read More
ሁለት ኢትዮጵያዊያን በግድያ ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ዋሉ

ሁለት ኢትዮጵያዊያን በግድያ ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ዋሉ

በሳዑዲ አረቢያ ሁለት ኢትዮጵያውያን አንድ ህንዳዊ በመግደል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገልጿል። የሳዑዲ አረቢያ ባለሥልጣናት በቅርቡ በጂዳ ከተማ 'አንድ ህንዳዊ ዜጋ ላይ ተኩስ ከፍተው ገድለዋል' ተብለው የተጠረጠሩ ሁለት ኢትዮጵያውያን ዜጎችን በቁጥጥር ሥር ማዋላቸውን አስታውቀዋል፡፡ የጂዳ ግዛት ፖሊስ ባወጣው መግለጫ፤ የሀገሪቱን የድንበር ደህንነት ደንቦች በመጣስ በሕገ-ወጥ መንገድ በሚኖሩ ሁለት ኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ ክስ መመስረቱን አስታውቋል። በከተማዋ አቅራቢያ በሚገኝ ተራራማ አካባቢ ሕገ-ወጥ ዕፅ በመገበያያት ላይ በነበሩ ሰዎች መካከል በተፈጠረ ጠብና አለመግባባት ሳቢያ ህንዳዊው ግለሰብ በጥይት መመታቱን ገልፍ ኒውስ ዘግቧል፡፡ በዚህም በግጭቱ ወቅት ከተጠርጣሪዎቹ አንዱ ኢትዮጵያዊ በህንዳዊው ተጎጂ ላይ ተኩስ ከፍቶ ጉዳት እንዳደረሰበት የገለጸው ፖሊስ፤ በጥይት የተመታው ግለሰብ ወዲያውኑ በአቅራቢያው ወደሚገኝ ሆስፒታል ቢወሰድም፣…
Read More
ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችው በህወሀት ምክንያት መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ተናገሩ

ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችው በህወሀት ምክንያት መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ተናገሩ

የሀገር መከላከያ ሰራዊት አዛዥ ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሰሜን እዝ ላይ የተፈጸመውን ጥቃት ለማሰብ በሚል በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ህወሀትን ተችተዋል። ፊልድ ማርሻል በዚህ ጊዜ እንዳሉት መከላከያ ሠራዊት ሕይወቱን ከሰጠለት ሕዝብ ውስጥ የወጡ ጥቂት ካሃዲዎች ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ከኋላው መውጋታቸው ሕመሙ ጥልቅ ነው ብለዋል። በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈፀመው ክህደት ወንድም ወንዱሙ ላይ የፈፀመው ክህደት በመሆኑ በታሪክ ልዩ እንደሚያደርገውም ጠቅሰዋል። የትግራይ ሕዝብ በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመውን ክህደት አይቀበለውም ያሉት አዛዡ  የትግራይ ሕዝብ በልጆቹ ክህደት አፍሮ፣ ተመልሰን መቐለ ስንገባ አጨብጭቦ ተቀብሎን ነበር ሲሉም አክለዋል። ስለዚህ ክህደት እና አስነዋሪ ታሪክ ስናውራ ስለ ጥቂት የሕወሓት አመራሮች እንጂ ስለ ትግራይ ሕዝብ እንዳልሆነም ገልጸዋል። የህወሀት…
Read More
በኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈጸሙት ጥቃቶች እንዲመረመሩ ለዓለማቀፉ ማሕበረሰብ ጥሪ ቀረበ

በኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈጸሙት ጥቃቶች እንዲመረመሩ ለዓለማቀፉ ማሕበረሰብ ጥሪ ቀረበ

አምስት ፓርቲዎች የመሰረቱት 'ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት' የተሰኘው ቅንጅት፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈጸሙት ጥቃቶች እንዲመረመሩ ለዓለማቀፉ ማሕበረሰብ ጥሪ አቅርቧል፡፡ ቅንጅቱ በቅርቡ  በአርሲ የተፈጸመውን ግድያ አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፤“ በኢትዮጵያ የሚፈጸሙት ማንነትና ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች መንግሥታዊ መዋቅርን የተከተሉ፣ ሥርዓታዊና ተጨማሪ እጅ ያለበት ስለመኾኑ ምርመራ እንዲደረግ ” ጥሪውን አቅርቧል። ቅንጅቱ፤ “ጠያቂም ተጠያቂም ባለመኖሩ መግደል ቀላል ኾኗል” በሚል  ያወጣው መግለጫ፤ “ እንዲህ ዓይነቱን ግዙፍ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት" በጽኑ እንደሚያወግዝ አስታውቆ፣ "እልቂት የየቀን ገጠመኙ ለኾነው የአካባቢው ማኅበረሰብም" ብርታትና መጽናናትን ተመኝቷል። መላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ አንድነት ፓርቲ (ኢሕአፓ)፣ እናት ፓርቲ፣ አዲሲ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አኢዴፓ) እና አማራ ግዮን ንቅናቄ ( አግን) የመሠረቱት ' ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት…
Read More
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጠና እድል ምርቶቿን ወደ ሶስት ሀገራት እየላከች ነው ተባለ

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጠና እድል ምርቶቿን ወደ ሶስት ሀገራት እየላከች ነው ተባለ

ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጠና ስምምነትን መስከረም 29 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ መጀመሯ ይታወሳል። ሀገሪቱ ምርቶቿን ወደ ሶስት የአፍሪካ ሀገራት በመላክ ላይ ነች የተባለ ሲሆን ምርቶቹ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎ በኩል እየተላኩ እንደሆነም ተገልጿል። የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ወንድሙ ፍላቴ እንዳሉት ከተላኩት የመጀመሪያ የወጪ ንግድ ምርቶች መካከል ስጋ፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ ቡና እና ጥራጥሬ እህሎች ይገኙበታል። ኬንያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሶማሊያና ጅቡቲ ደግኖ የኢትዮጵያ ምርቶሽ የተላከባቸው ሀገራት እንደሆኑ ተጠቅሷል። ምርቶቹ በአብዛኛው የተጓጓዙት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎ አማካኝነት ሲሆን፤ አየር መንገዱ ለነፃ ንግድ ቀጠናው ትግበራ ትልቁን ድርሻ እየተወጣ ነው ብለዋል አቶ ወንድሙ። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጠና ስምምነትን…
Read More
ቋሚ ሲኖዶሱ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የተፈጸመውን የ25 ምዕመናን ግድያ አወገዘ

ቋሚ ሲኖዶሱ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የተፈጸመውን የ25 ምዕመናን ግድያ አወገዘ

በኦሮሚያ ክልል በምሥራቅ አርሲ ዞን አስተዳደር በጉና፣ በመርቲ፤ በሸርካ እና በሆሎንቆ ዋቢ ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች ላይ ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች የተፈጸሙትን አሰቃቂ ግድያዎች የቤተክርሲቲያኒቷ ቋሚ ሲኖዶስ አውግዟል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖችን አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል፡፡ በመግለጫውም ጥቅምት 14 ለ15 ቀን 2018 ዓ.ም በጉናና መርቲ ወረዳዎች 17 ክርስቲያኖች፣ ጥቅምት 17 ለ18 ቀን 2018 ዓ.ም. በሸርካ ወረዳ 3 ክርስቲያኖች እንዲሁም ጥቅምት 18 ለ19 ቀን 2018 ዓ.ም. በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 5 ክርስቲያኖች በድምሩ በጥቅምት ወር 2018 ዓ.ም. ብቻ 25 ኦርቶዶክሳውያን በድንገት ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን አስታውቋል፡፡ ግድያውም…
Read More
የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጸብ ባንድ ጀምበር የመጣ እንዳልሆነ ጠቅላይ ሚንስትሩ ተናገሩ

የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጸብ ባንድ ጀምበር የመጣ እንዳልሆነ ጠቅላይ ሚንስትሩ ተናገሩ

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ በዛሬው ዕለት ከፓርላማ አባላት ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ከኤርትራ ጋር የተፈጠረው አለመግባባት በአንድ ጀምበር የመጣ ሳይሆን ቀስ በቀስ በሂደት መምጣቱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመት በፊት የባህር ሀይሏን እንዳቋቋመች የተናገሩት ጠቅላይ ሚንስትሩ ይህ ሀይል የተቋቋመው በሀገር ውስጥ ብቻ እንዲገታ በማሰብ አልነበረም አሰብ ወደብን ከኤርትራ እንደምንረከብ በማመን ነበር ብለዋል። "ከኤርትራ መንግሥት ጋር ተስማምተን ከዚህ ወደ አሰብ የሚወስደውን መንገድ ጠግነናል ፣እንከፍታለን ብለን ጠግነናል፣ መንገዱን ከጠገንን በኋላ ግን ችግር አለብን አሰብ ወደብ ተዳክሟል አሉን። አንዳንድ ሰው ከኤርትራ ጋር የገባንበት አለመግባባት በአንድ ምሽት የመጣ ይመስለዋል እንደዛ አይደለም ታሪኩን ስለማንናገር ነው" ብለዋል ጠቅላይ ሚንስትር አብይ። ወደ አሰብ መንገድ ጠግነን ከጨረስን በኃላ '…
Read More
በኢትዮጵያ የባንኮች የገንዘብ ዝውውር ቅናሽ ማሳየቱ ተገለጸ

በኢትዮጵያ የባንኮች የገንዘብ ዝውውር ቅናሽ ማሳየቱ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ በባንክ የሚካሄድ አጠቃላይ የገንዘብ ዝውውር ቅናሽ ማሳየቱን የኢትዮጵያ ምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች ማኅበር "ባካሄድኩት ጥናት አረጋግጫለሁ" ብሏል። በማኅበሩ ከፍተኛ የምጣኔ ሃብት ተመራማሪ ናስር የኑስ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ በተለይ ከ2012 ዓ.ም. መጨረሻ ወራት አንስቶ፣ በይበልጥ ደግሞ ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ የገንዘብ ዝውውር (ትራንዛክሽን ባንኪንግ) አገልግሎት የሚጠቀሙ ደንበኞች ቁጥር እየቀነሰ ነው። ለዚህ የገንዘብ ዝውውር መቀነስ ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው ያሏቸውን ጉዳዮች የጠቀሱት የምጣኔ ሃብት ተመራማሪው፤ የዜጎች የገቢ ማሽቆልቆል፣ አልፎ አልፎ የሚታዩ ግጭቶችና ጦርነቶች እልባት አለማግኘት፣ የሥራ አጥ ቁጥር መጨመር፣ እና የኢንተርኔት አገልግሎት ችግር እንደሆኑ ዘርዝረዋል። ተመራማሪው ይህንን እያሽቆለቆለ ያለውን የገንዘብ ዝውውር ለማነቃቃት ባንኮች ሊተገብሯቸው ይገባል ካሏቸው የመፍትሔ እርምጃዎች መካከል፤ ባንኮች ለገንዘብ ዝውውር…
Read More
ትዕግሥት አሰፋ እና ዮሚፍ ቀጄልቻ የዓመቱ ምርጥ አትሌት ዕጩ ሆኑ

ትዕግሥት አሰፋ እና ዮሚፍ ቀጄልቻ የዓመቱ ምርጥ አትሌት ዕጩ ሆኑ

የዓለም አትሌቲክስ በሁለቱም ፆታ የ2025 የዓመቱ የጎዳና ላይ ምርጥ አትሌት ዕጩዎችን ይፋ አድርጓል። በዚህም ኢትዮጵያ አትሌት ትዕግሥት አሰፋ እና ዮሚፍ ቀጄልቻን በዓመቱ በሁለቱም ፆታ ምርጥ ብቃት ካሳዩ አምስት አትሌቶች መካከል ተብለው እጩ ሆነዋል። በሴቶቹ አትሌት ትዕግሥት አሰፋ ከኬንያውያኑ አትሌቶች ፔሬስ ጄፕቺርቺር እና አግኔስ ንጌቲች፣ ለኔዘርላንድስ ከምትሮጠው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሲፈን ሀሰን እና ከስፔናዊቷ ማሪያ ፔሬዝ ጋር ምርጥ አምስት ውስጥ መግባት ችላለች። በወንዶቹ ደግሞ አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ከብራዚላዊው አትሌት ካይኦ ቦንፊን፣ ካናዳዊው አትሌት ኢቫን ዱንፊ፣ ኬንያዊው አትሌት ሳባስቲያን ሳዌና ከታንዛኒያዊው አልፎንስ ሲምቡ ጋር ምርጥ አምስት መግባት ችሏል። በለንደን ማራቶን አሸናፊ የነበረችው አትሌት ትዕግሥት አሰፋ በውድድር ዓመቱ በተካሄደው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና 2ኛ…
Read More