Athletics

አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ የሮጠበት ማልያ በ2400 ዶላር ተሸጠ

አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ የሮጠበት ማልያ በ2400 ዶላር ተሸጠ

በበርካታ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ ስኬታማ አትሌት የሆነው ሀይሌ ገብረስላሴ የሮጠበት አንድ ማልያ በ2 ሺህ 400 ዶላር ተሸጧል፡፡ በአዲስ አበባ በተካሄደ በዚህ ጨረታ ላይ የቀረበው ይህ ማልያ አትሌት ሀይሌ በ1992 በደቡብ ኮሪያ ሴኡል ከተማ በተካሄደው የ10 ሺህ ሜትር ውድድርን ያሸነፈበት ማልያ ነበር፡፡ ይህ ውድድር ለአትሌት ሀይሌ ገብረ ስላሴ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የጀመረበት ወቅት እንደነበርም ተገልጿል፡፡ የታላቁ ሩጫ መስራች እና ባለቤት አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ ለጨረታ ቀርቦ 2 ሺሕ 400 ዶላር የተሸጠው ማልያ የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን ለማጠናከር ይውላልም ተብሏል፡፡ በጨረታው የታላቁ ሩጫ ባዘጋጀው የእራት ግብዣ ፕሮግራም ላይ የኃይሌ ገ/ሥላሴ የሮጠበት ማልያ፤ በእንግሊዛዊ ተጋባዥ እንግዳ አሸንፏል። ይህንን የማልያ ጨረታ እንግሊዛዊ ዜግነት ያለው…
Read More
ኢትዮጵያ በዓለም ወጣቶች አትሌቲክስ ውድድር አራት የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

ኢትዮጵያ በዓለም ወጣቶች አትሌቲክስ ውድድር አራት የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

በደቡብ አሜሪካዋ ፔሩ ሊማ ከተማ ሲካሄድ የነበረው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ውድድር ትናንት ጠናቋል፡፡ በዚህ የአትሌቲክ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ከአሜሪካ በመቀጠል ከዓለም ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች፡፡ ኢትዮጵያን በመወከል የተሳተፈው ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ብሔራዊ ቡድን በ6 ወርቅ፣ 2 ብር እና 2 ነሐስ በአጠቃላይ 10 ሜዳሊያዎችን ማሸነፍ ችሏል። በዚህ ኢትዮጵያ ከዓለም አሜሪካን በመከተል 2ኛ እንዲሁም ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን ያጠናቀቀች ሲሆን፤ ውድድሩን 1ኛ ደረጃ በመያዝ ያጠናቀቀች አሜሪካ በ8 ወርቅ፣ 4 ብር እና 4 ነሃስ በድምሩ 16 ሜዳሊያዎችን አግኝታለች። ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኙ አትሌቶች በአትሌት መዲና ኢሳ በ5000 ሜትር፣ በአትሌት ሲምቦ አለማየሁ በ3000 ሜትር መሰናክል በአትሌት ጀነራል ብርሃኑ በ800 ሜትር፣ በአትሌት…
Read More
መዲና ኢሳ በሴቶች የ5 ሺህ ሜትር ውድድር የወርቅ ሜዳሊያ አሸነፈች

መዲና ኢሳ በሴቶች የ5 ሺህ ሜትር ውድድር የወርቅ ሜዳሊያ አሸነፈች

የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ውድድር ትናንት በደቡብ አሜሪካዊቷ ሀገር ፔሩ ተጀምሯል፡፡ ኢትዮጵያ በዚህ ውድድር ላይ እየተሳተፉ ካሉ ሀገራት መካከል አንዷ ስትሆን በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ አትሌቶችን ከቀናት በፊት ወደ ሊማ ልካለች፡፡ እስካሁን በሁለቱም ጾታዎች የ5 ሸህ ሜትር ፍጻሜ ውድድር የተካሄደ ሲሆን ኢትዮጵያዊያን በሁለቱም ጾታ ሜዳሊያ ውስጥ ገብተዋል፡፡ በ5000 ሜትር የሴቶች የፍጻሜ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አንደኛ እና ሁለተኛ ሆነው አሸንፈዋል፡፡ አትሌት መዲና ኢሳ ውድድሩን በ14 ደቂቃ 39 ሰከንድ 71 ማይክሮ ሰከንድ በመጨረስ አንደኛ በመውጣት ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝታለች። አትሌቷ ውድድሯን ያጠናቀቀችው በገንዘቤ ዲባባ ተይዞ የነበረውን ሪከርድ በ28 ሰከንዶች በማሻሻል ነው። ከሁለት ሳምንት በፊት በተጠናቀቀው የፓሪስ ኦሎምፒክ ላይ ሰባተኛ ደረጃን ይዛ…
Read More
ኢትዮጵያን በፔሩ ከ20 ዓመት በታች ዓለም አቀፍ ውድድር ላይ የሚወክለው አትሌት በጥይት ተመታ

ኢትዮጵያን በፔሩ ከ20 ዓመት በታች ዓለም አቀፍ ውድድር ላይ የሚወክለው አትሌት በጥይት ተመታ

የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ውድድር ከአንድ ሳምንት በኋላ በላቲን አሜሪካዋ ፔሩ አዘጋጅነት ይካሄዳል፡፡ ለሶስት ቀናት በሚካሄደው በዚህ ውድድር ላይ ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች ተመርጠው የመጨረሻ ልምምድ በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለውድድሩ ከመረጣቸው አትሌቶች መካከል የ17 አመቱ አትሌት ሰው መሆን ታሪኩ አንዱ ነው፡፡ ይህ አትሌት ባሳለፍነው እሁድ ነሀሴ 5 ቀን 2016 ዓም የከሰዓት በኋላ ልምምድ ለመስራት ወደ ጫካ ወጣ ብሎ ልምምዱን ጨርሶ እያቀዘቀዘ ባለበት ያልታሰበ ሰው ጥቃት አድርሶበታል ተብሏል፡፡ አትሌቱን አንድ ሰው ከቀረበው በኋላ ፓሊስ ነኝ በማለት ራሱን ካስተዋወቀው በኋላ እዚህ አካባቢ ቁማር የሚጫወቱ ታውቃለህ በማለት ሲጠይቀው አላውቅም ብሎ እንደመለሰ ነገር ግን ወዲያው በፎጥነት ይህ ሰው አንገቱን ሲይዘው አትሌቱም…
Read More
የማራቶን አትሌቶች አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ ኢትዮጵያ የሸለመቻቸውን 2 ሚሊዮን ብር አልቀበልም አሉ

የማራቶን አትሌቶች አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ ኢትዮጵያ የሸለመቻቸውን 2 ሚሊዮን ብር አልቀበልም አሉ

በፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ልዑክ ቡድን በብሄራዊ ቤተ መንግስት አቀባበል እና የእራት ግብዣ ተደርጎለታል። ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በተገኙበት በተካሄደው የአቀባበል እና የአውቅና ስነ ስርዓት ላይም ለአትሌቶች፣ አሰልጣኞች እና ለታሳታፊዎችዎች እንደየ ተሳትፏቸው እና አብርክቷቸው ከ50 ሺህ ብር እስከ 7 ሚሊየን ብር የገንዘብ ሽልማት ተሰጥቷል። በዚህ ስነ ስርዓት ላይ በማራቶን ለኢትዮጵያ ብቸኛውን ወርቅ ሜዳሊያ ላስገኘው አትሌት ታምራት ቶላ 7 ሚሊየን ብር እና ወርቅ ኒሻን ሽልማት ተበርክቶለታል። የብር ሜዳልያ ላመጡት አትሌት ትግስት አሰፋ፣ አትሌት በሪሁን አረጋዊ እና አትሌት ፅጌ ዱጉማ ለእያንዳንዳቸው የ 4 ሚሊዮን ብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የታምራት ቶላ እና ትግስት አሰፋ አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ በስነ ስርዓቶ ላይ የ2 ሚልዮን ብር…
Read More
አትሌት ቀነኒሳ በቀለ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ የአፍሪካ ስፖርተኛ ተብሎ ተመረጠ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ የአፍሪካ ስፖርተኛ ተብሎ ተመረጠ

የአሜሪካው አለምአቀፍ የስፓርት ቻናል (ኢኤስፒኤን) ቀነኒሳ በቀለን የ21ኛው ክፍለዘመን ምርጥ አትሌት ነው ሲል መርጦታል፡፡ የስፖርት ቻናሉ ከቀነኒሳ በቀለ በተጨማሪ ሌላኛዋ ኢትዮጵያት አትሌት ጥሩነሽ ዲባባን ጨምሮ በ21ኛው ክፍለዘመን ምርጥ ያላቸውን የአፍሪካ ስፓርተኞች ይፋ አድርጓል። ኢኤስፒኤን አህጉሪቱ ካላት ስፋት እና የስፖርት ብዛት አንጻር 25 ምርጥ አትሌቶችን መምረጥ ከባድ መሆኑን አስታውቋል። ዓለም ካየቻቸው ምርጥ የማራቶን ሯጭ አንዱ ከሆነው ኢሉድ ኪፕቾጌ እና ኦሎምፒክ እና በርካታ የአውሮፓ ሻሜፒዮን ሽፕ አሸናፊ ከሆነው ሳሙኤል ኢቶ ማንን ትመርጣላችሁ? ሲልም ኢኤስፒኤን ይጠይቃል። አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በቻናሉ ዘገባ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ የአፍሪካ ስፖርተኛ ተብሎ ስሙ በመካተቱ እንደተደሰተ በማህበራዊ ትስስር ገጾቹ ላይ ጽፏል። አትሌት ቀነኒሳ በ2000ዎቹ በ10ሺ እና በ5ሺ ሜትር…
Read More
ኢትዮጵያ በመላው አፍሪካ አትሌቲክስ ውድድር አራተኛ ሆና አጠናቀቀች

ኢትዮጵያ በመላው አፍሪካ አትሌቲክስ ውድድር አራተኛ ሆና አጠናቀቀች

በካሜሩን አስተናጋጅነት የተካሄደው የመላው አፍሪካ አትሌቲክስ ውድድር ተጠናቋል፡፡ በካሜሩን ዋና ከተማ ዱዋላ አስተናጋጅነት ከ27 ሃገራት በላይ የተውጣጡ 2500 አትሌቶች ላለፉበት 6 ቀናት ሲሳተፉበት የነበረው 23ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ተጠናቋል። በዚህ ውድድር ለይ የተሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን አራተኛ ሆኖ አጠናቋል፡፡ ኢትዮጵያ በአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና 5 ወርቅ፣ 4 የብር እና አንድ የነሐስ በድምሩ 10 ሜዳሊያዎችን አግኝቷል፡፡ ኢትዮጵያጵያ በውድድሩ ላይ 68 አትሌቶችን በ19 የአትሌቲክስ የውድድር አይነቶች ላይ የተሳተፈች ሲሆን ከናይጀሪያ በመቀጠል አራተኛ ሆና አጠናቃለች፡፡ የወርቅ ሜዳልያ ለኢትዮጵያ ያስገኙ አትሌቶች ፋንታዬ በላይነህ በ5ሺ ሜትር ሴቶች ፣ንብረት መላክ በ10ሺ ሜትር ወንዶች ፣ምስጋና ዋቁማ በወንዶች በ20 ኪሎ ሜትር እርምጃ፣    ስንታየሁ ማስሬ በሴቶች በ20 ኪሎ ሜትር…
Read More
ኢትዮጵያ በግላስኮው የዓለም ቤት ውስጥ አትሌቲክስ ውድድርን በአምስተኛነት አጠናቀቀች

ኢትዮጵያ በግላስኮው የዓለም ቤት ውስጥ አትሌቲክስ ውድድርን በአምስተኛነት አጠናቀቀች

በስኮትላንድ ግላስጎ ሲካሄድ የቆየው የ2024 የአለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ፍጻሜውን አግኝቷል። ከየካቲት 22 እስክ 24 2016 ዓ.ም ሲካሄድ በነበረው የ19ኛው የዓለም የቤት ዉስጥ ሻምፒዮና ከ130 በላይ ሀገራት  የተውጣጡ ከ650 በላይ አትሌቶቸ  መሳተፋቸው ተነግሯል። ኢትዮጵያ በ800 ሜትር፣ በ1500 ሜትር እና በ3000 ሜትር  በሴትና በወንድ  በአጠቃላይ  በ8 ሴቶች እና በ5 ወንዶች በድምሩ በ13 አትሌቶች መሳተፏን ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በሻምፒዮናው በሴቶች 800 ሜትር ፅጌ ዱጉማ እና በሴቶች 1500 ሜትር ፍሬወይኒ ሀይሉ የወርቅ፣ በሴቶች 3000 ሜትር ጉዳፍ ፀጋዬ የብር እንዲሁም በወንዶች 3000 ሜትር ሰለሞን ባረጋ የነሃስ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ ያስገኙ አትሌቶች ሆነዋል። በዚህ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ  ሁለት ወርቅ አንድ ነሀስ በአንድ ብር…
Read More
የቫሌንሲያ ማራቶን ውድድር በኢትዮጵያዊያን የበላይነት ተጠናቀቀ

የቫሌንሲያ ማራቶን ውድድር በኢትዮጵያዊያን የበላይነት ተጠናቀቀ

በስፔኗ ቫሌንሲያ የተካሄደው የማራቶን ውድድር በኢትዮጵያዊያን የበላይነት ተጠናቀቀ፡፡ ኢትዮጵያዊያን በተደጋጋሚ የሚነግሱባት የስፔኗ ቫሌንሲያ ዛሬም ኢትዮጵያዊያን ተመሳሳይ ድሎችን አግኝተውባታል፡፡ በዚው ውድድር በሁለቱም ጾታዎች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በአንደኝነት አጠናቀዋል፡፡ በሴቶች የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊያን ከአንደኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ በበላይነት ሲያሸንፉ አትሌት ውርቅነሸ ደገፈ፣ አልማዝ አያና እና ህይወት ገብረኪዳን ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ጠናቀዋል፡፡ በዚህ የወንዶች የማራቶን ውድድር ላይ አትሌት ሲሳይ ለማ አንደኛ፣ ኬንያዊው አትሌት አሌክሳንደር ሙቲሶ ሁለተኛ እንዲሁም ዳዊት ወልዴ እና ቀነኒሳ በቀለ ሶተኛ እና አራተኛ ሆነው አጠናቀዋል፡፡ አትሌት ሲሳይ ለማ ርቀቱን 2:01:48 በሆነ ሰአት ማጠናቀቅ የቻለ ሲሆን የቦታውን ክብረወሰን ማሻሻል ሲችል ተጠብቆ የነበረው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ አራተኛ ሆኖ ማጠናቀቅ ችሏል፡፡…
Read More
አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ ገለጸ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ ገለጸ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ሕዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም በሚካሄደው የቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ አስታውቋል፡፡ አትሌቱ በፌስቡክ ገጹ እንዳለው "ከብዙ ጊዜ ጉዳት በኋላ በቫሌንሺያ ማራቶን እሳተፋለሁ" ብሏል። "ከብዙ ጉዳት በኋላ ወደ ውድድር በመመለሴ ደስተኛ ነኝ" ያለው አትሌት ቀነኒሳ አኤኤንቲኤ የተሰኘው ኩባንያ ስፖንሰሬ ነው፣ ላደረገልኝ ድጋፍ አመሰግናለሁ " ሲልም ገልጿል። ውድድሩ የፊታችን ሕዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም በስፔኗ ቫሌንሲያ እንደሚካሄድ ተገልጿል። አትሌት ቀነኒሳ በአምስት እና አስር ሺህ ውድድሮች ላይ ለዓመታት ሳይረታ የቆየ ውጤታማ አትሌት ሆኖ ቆይቷል። በሁለቱም ርቀቶች የዓለም ሪከርዶችን ለ16 ዓመታት ይዞ የቆየው አትሌት ቀነኒሳ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ፊቱን ወደ ማራቶን ውድድር አዙሯል። የማራቶን ውድድርን ከሁለት ሰዓት በታች ይገባል ተብሎ ከሚጠበቁት…
Read More