Athletics

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ ገለጸ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ ገለጸ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ሕዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም በሚካሄደው የቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ አስታውቋል፡፡ አትሌቱ በፌስቡክ ገጹ እንዳለው "ከብዙ ጊዜ ጉዳት በኋላ በቫሌንሺያ ማራቶን እሳተፋለሁ" ብሏል። "ከብዙ ጉዳት በኋላ ወደ ውድድር በመመለሴ ደስተኛ ነኝ" ያለው አትሌት ቀነኒሳ አኤኤንቲኤ የተሰኘው ኩባንያ ስፖንሰሬ ነው፣ ላደረገልኝ ድጋፍ አመሰግናለሁ " ሲልም ገልጿል። ውድድሩ የፊታችን ሕዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም በስፔኗ ቫሌንሲያ እንደሚካሄድ ተገልጿል። አትሌት ቀነኒሳ በአምስት እና አስር ሺህ ውድድሮች ላይ ለዓመታት ሳይረታ የቆየ ውጤታማ አትሌት ሆኖ ቆይቷል። በሁለቱም ርቀቶች የዓለም ሪከርዶችን ለ16 ዓመታት ይዞ የቆየው አትሌት ቀነኒሳ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ፊቱን ወደ ማራቶን ውድድር አዙሯል። የማራቶን ውድድርን ከሁለት ሰዓት በታች ይገባል ተብሎ ከሚጠበቁት…
Read More
ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ድል አደረጉ

ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ድል አደረጉ

የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ በላቲቪያ ሪያ በመደረግ ላይ ሲሆን የወንዶች እና የሴቶች የ5 ሺህ ሜትር ውድድር ፍጻሜውን አግኝቷል። በወንዶች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ተከታትለው በመግባት ውድድሩን አጠናቀዋል። አትሌት ሀጎስ ገብረ ህይወት 12:59 በሆነ ሰዓት ውድድሩን በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ ደግሞ በ13:02 በመግባት ሁለተኛ ሆኖ አጠናቋል። ኢትዮጵያዊው አትሌት ሀጎስ ገብረ ህይወት የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ የወንዶች 5ኪ.ሜ ውድድርን ማሸነፍ የቻለ የመጀመሪያው አትሌት ሆኗል። በሴቶች ተመሳሳይ ርቀት ውድድር ኬንያዊያኑ አትሌት ቺቤት አንደኛ እንዲሁም ናሬንጉሩክ ሁለተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ኢትዮጵያዊያኑ አትሌቶች እጅጋየሁ ታዬ እና መዲና ኢሳ ደግሞ ሶስተኛ እና አራተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። በሌላ የ1 ማይል ርቀት ውድድር ደግሞ አትሌት ድርቤ ወልተጂ ኬንያዊቷን የ 1500ሜ…
Read More
አትሌት ደራርቱ ቱሉ የአፍሪካ አትሌቲክስ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆና ተመረጠች

አትሌት ደራርቱ ቱሉ የአፍሪካ አትሌቲክስ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆና ተመረጠች

አትሌት ደራርቱ ቱሉ የአፍሪካ አትሌቲክስ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆና ተመረጠች የኮንፌዴሬሽን ኦፍ አፍሪካ አትሌቲክስ ኮንግረስ በዛምቢያ መዲና ሉሳካ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት የሆነችው አትሌት ደራርቱ ቱሉ የአፍሪካ አትሌቲክስን በምክትል ፕሬዚዳንትነት እንድትመራ ተመርጣለች፡፡ በዚህም ካውንስሉ ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉን የአፍሪካ አትሌቲክስን በምክትል ፕሬዝዳንትነት እንድትመራ በሙሉ ድምጽ መመረጧን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡ የ51 ዓመቷ አትሌት ደራርቱ ሀገሯን እና ራሷን ያስጠራችባቸው በርካታ ሜዳሊያዎችን ያሸነፈች ሲሆን በኦሎምፒክ የ10 ሺህ ሜትር ርቀት ውድድር ታሪክ የወርቅ ሜዳሊያ ያመጣች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ተብላለች፡፡ አትሌት ደራርቱ ከ2018 ጀምሮ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን ከቀድሞው ፕሬዝዳንት አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ ተረክባ በመምራት ላይ ትገኛለች፡፡ አትሌቷ ባሳካቻቸው በርካታ ውድድሮች ለሌሎች ታዳጊ አትሌቶች…
Read More
ሞ ፋራህ የፖርት-ጄንቲል 10 ኪሎ ሜትር ውድድርን በሰባተኛነት አጠናቀቀ

ሞ ፋራህ የፖርት-ጄንቲል 10 ኪሎ ሜትር ውድድርን በሰባተኛነት አጠናቀቀ

በሳሙኤል አባተ ሞ ፋራህ በፖርት-ጄንቲል 10 ኪሎ ሜትር ውድድርን በሰባተኛነት አጠናቀቀ። ሞ ፋራህ የጋቦን ፖርት-ጄንቲል 10 ኪሎ ሜትር ሩጫ በ30 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ ሰባተኛ ሆኖ አጠናቋል። የአራት ጊዜ የኦሎምፒክ ሻምፒዮን የሆነው ሞ ፋራህ ከሁለት ሳምንታት በኋላ ለሚካሄደው የለንደን ማራቶን ውድድር በኢትዮጵያ ልምምዱን አድርጓል ተብሏል። አትሌቱ 2023 ጡረታ ከመውጣቱ በፊት የመጨረሻው የውድድር ዓመቱ እንደሚሆን ባለፈው በጥር ወር አስታውቋል። ጋቦን ላይ ኬንያዊው ቪንሴንት ኪፕኬሞይ በ28 ደቂቃ ከ11 ሰከንድ አንደኛ በመውጣት አሸንፏል። ፋራህ እ.ኤ.አ. በ2022 የለንደን ማራቶን በሽንጥ ጉዳት ምክንያት ያልተሳተፈ ሲሆን፤ የዘንድሮው ውድድር ከ2019 በኋላ የመጀመሪያው ሙሉ ማራቶን ይሆናል ተብሏል። ለብሪታኒያዊው የመጨረሻ የለንደን ማራቶን ውድድር እንደሚሆን የሚጠበቅ ሲሆን፤ ቀነኒሳ በቀለን ጨምሮ በታሪክ…
Read More
የሎስ አንጀለስ ማራቶን በኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸናፊነት ተጠናቀቀ

የሎስ አንጀለስ ማራቶን በኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸናፊነት ተጠናቀቀ

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተለያዩ ሀገራት በተካሄዱ የማራቶን ውድድሮችን አሸነፉ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተለያዩ ሀገራት በተካሄዱ የማራቶን ውድድሮች ድል ማስመዝገብ ችለዋል። በቻይና ሸንዤን በተደረገ ማራቶን በሁለቱም ጾታ ኢትዮጵያውያኑ ድል የቀናቸው ሲሆን፤በወንዶች አትሌት ባንታየሁ አዳነ በሴቶች አገሬ ታምር በአንደኝነት አጠናቀዋል። በአሜሪካ ሎሳንጀለስ በተካሄደ የወንዶች ማራቶን አትሌት ጀማል ይመር ቀዳሚ መሆን ሲችል ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት የማነ ጸጋዬ ደግሞ ሁለተኛ ሆኖ ውድድሩን ጨርሷል። በባርሴሎና በተደረገ የማራቶን ውድድርም ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ዘይነባ ይመር ውድድሩን በአንደኝነት ስታጠናቅቅ በአሜሪካ የኒዮርክ ግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ ደግሞ በሴቶች አትሌት ሰንበሬ ተፈሪ ሁለተኛ ሆና ውድድሯን አጠናቃለች። በታይዋን ታይፔ በተደረገው የሴቶች ማራቶን ውድድርም በቀለች ጉደታ፣ መሰረት ድንቄ እና ገበያነሽ አየለ ከአንድኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃን…
Read More
ኢትዮጵያዊው አበበ ቢቂላን ለማሰብ ሮም ላይ በባዶ እግሩ ሊሮጥ መሆኑን አስታወቀ

ኢትዮጵያዊው አበበ ቢቂላን ለማሰብ ሮም ላይ በባዶ እግሩ ሊሮጥ መሆኑን አስታወቀ

የፊታችን እሁድ መጋቢት 10 ቀን 2015 ዓ.ም የ2023 የሮም ማራቶን ይካሄዳል። በዚህም ማራቶን ታሪክ ራሱን ይደግማል የተባለ ሲሆን ኢትዮጵያዊው የባዶ እግር ሯጭ እንዲሁም ለረጅም አመታት በኢትዮጵያ ታላቁ ሩጫ ቁልፍ ዳይሬክተር በመሆን የሰራው የ45 ዓመቱ ኤርሚያስ አየለ ሙሉ ማራቶን በባዶ እግሩ ይሮጣል። ኤርሚያስ አየለ ይህንን የሚያደርገው ለኢትዮጵያው ታላቅ አትሌት አበበ ቢቂላ ክብር እንዲሁም ለሀገር ገፅታ ግንባታ ሲል ነው። " አበበ ቢቂላ በኦሎምፒክ ጨዋታዎች የወርቅ ሜዳሊያ በማግኘት የመጀመሪያው ጥቁር በመሆኑ ለኢትዮጵያውያን አትሌቶች ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ ለአፍራካውያን ስኬት መሰረት ጥሏል " የሚለው ኤርሚያስ " ሆኖም ግን ለሰራው ታሪክ የሚገባውን ያህል እውቅና እንዳላገኘ ይሰማኝ ነበር " ብሏል። ኤርሚያስ ፤ የአትሌት አበበ ቢቃላ ታሪክ ሁሌም…
Read More