29
Nov
አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ሕዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም በሚካሄደው የቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ አስታውቋል፡፡ አትሌቱ በፌስቡክ ገጹ እንዳለው "ከብዙ ጊዜ ጉዳት በኋላ በቫሌንሺያ ማራቶን እሳተፋለሁ" ብሏል። "ከብዙ ጉዳት በኋላ ወደ ውድድር በመመለሴ ደስተኛ ነኝ" ያለው አትሌት ቀነኒሳ አኤኤንቲኤ የተሰኘው ኩባንያ ስፖንሰሬ ነው፣ ላደረገልኝ ድጋፍ አመሰግናለሁ " ሲልም ገልጿል። ውድድሩ የፊታችን ሕዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም በስፔኗ ቫሌንሲያ እንደሚካሄድ ተገልጿል። አትሌት ቀነኒሳ በአምስት እና አስር ሺህ ውድድሮች ላይ ለዓመታት ሳይረታ የቆየ ውጤታማ አትሌት ሆኖ ቆይቷል። በሁለቱም ርቀቶች የዓለም ሪከርዶችን ለ16 ዓመታት ይዞ የቆየው አትሌት ቀነኒሳ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ፊቱን ወደ ማራቶን ውድድር አዙሯል። የማራቶን ውድድርን ከሁለት ሰዓት በታች ይገባል ተብሎ ከሚጠበቁት…