Parisolympic2024

በፓሪስ ኦሎምፒክ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን አዲስ አበባ ገባ 

በፓሪስ ኦሎምፒክ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን አዲስ አበባ ገባ 

ለ17 ቀናት በፓሪስ የተካሄደው 33ኛው ኦሎምፒክ ትናንት ማምሻውን ተጠናቋል። በፓሪስ ኦሎምፒክ ድል ያስመዘገቡ እና የተሳተፉ የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን ዛሬ ማለዳ ነሀሴ 7 ቀን 2016 ዓ.ም አዲስ አበባ ገብተዋል። የልኡካን ቡድኑ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በዛሬው እለት ከሰዓት በኋላ በብሔራዊ ቤተ-መንግስት ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ በተገኙበት ለልዑካን ቡድኑ የክብር ሽልማት፣ የማበረታቻ እና የእራት ግብዣ መርኃ-ግብር የሚካሄድ መሆኑንም ተገልጿል። ኢትዮጵያ በ33ኛው የፓሪስ ኦሊምፒክ 1 የወርቅ እና 3 የብር በአጠቃላይ 4 ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ ከዓለም 47ኛ ከአፍሪካ ደግሞ 4ኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቋ ይታወቃል። ታምራት ቶላ በማራቶን ወርቅ፣ ጽጌ ድጉማ በሴቶች 800 ሜትር ብር፣ በሪሁ አረጋዊ በወንዶች 10 ሺህ…
Read More
ኢትዮጵያ በፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

ኢትዮጵያ በፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

በየ አራት አመቱ አንዴ የሚካሄደው የኦሎምፒክ ውድድር በፓሪስ ሲካሄድ 15ኛ ቀኑን ይዟል። 206 ሀገራት በሚሳተፉበት በዘንድሮው ውድድር ከ10 ሺህ 500 በላይ አትሌቶችም እየተሳተፉበት ይገኛል፡፡ ዛሬ ረፋድ በተካሄደው የወንዶች ማራቶን ውድድር አትሌት ታምራት ቶላ ርቀቱን በ2:06:26 በሆነ ሰዓት አሸንፏል፡፡ አትሌት ታምራት ቶላ ውድድሩን የጨረሰበት ሰዓት አዲስ የኦሎምፒክ ክብረ ወሰን በማስመዝገብ እንዳሸነፈም ተገልጿል፡፡ ውድድሩን ቤልጂየማዊው በሽር አብዲ ሁለተኛ እንዲሁም ኬንያዊው ቤንሰን ኪፕሩቶ ደግሞ ሶስተኛ ሆነው አጠናቀዋል፡፡ አትሌት ታምራት ቶላ ከውድድሩ በኋላ እንዳለው "ውድድሩን በማሸነፌ እና የወርቅ ሜዳልያውን ለሀገሬ ኢትዮጵያ በማስገኘቴ በጣም በጣም ተደስቻለሁ" ሲል በእምባ ታጅቦ አስተያየቱን ሰጥቷል። አትሌት ታምራት ቶላ በውድድሩ በ2:06:26 በሆነ ሰዓት በመግባት በወንዶች ማራቶን የኦሎምፒክ ሪከርድ ባለቤት መሆን…
Read More
አትሌት ቀነኒሳ በቀለ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ የአፍሪካ ስፖርተኛ ተብሎ ተመረጠ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ የአፍሪካ ስፖርተኛ ተብሎ ተመረጠ

የአሜሪካው አለምአቀፍ የስፓርት ቻናል (ኢኤስፒኤን) ቀነኒሳ በቀለን የ21ኛው ክፍለዘመን ምርጥ አትሌት ነው ሲል መርጦታል፡፡ የስፖርት ቻናሉ ከቀነኒሳ በቀለ በተጨማሪ ሌላኛዋ ኢትዮጵያት አትሌት ጥሩነሽ ዲባባን ጨምሮ በ21ኛው ክፍለዘመን ምርጥ ያላቸውን የአፍሪካ ስፓርተኞች ይፋ አድርጓል። ኢኤስፒኤን አህጉሪቱ ካላት ስፋት እና የስፖርት ብዛት አንጻር 25 ምርጥ አትሌቶችን መምረጥ ከባድ መሆኑን አስታውቋል። ዓለም ካየቻቸው ምርጥ የማራቶን ሯጭ አንዱ ከሆነው ኢሉድ ኪፕቾጌ እና ኦሎምፒክ እና በርካታ የአውሮፓ ሻሜፒዮን ሽፕ አሸናፊ ከሆነው ሳሙኤል ኢቶ ማንን ትመርጣላችሁ? ሲልም ኢኤስፒኤን ይጠይቃል። አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በቻናሉ ዘገባ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ የአፍሪካ ስፖርተኛ ተብሎ ስሙ በመካተቱ እንደተደሰተ በማህበራዊ ትስስር ገጾቹ ላይ ጽፏል። አትሌት ቀነኒሳ በ2000ዎቹ በ10ሺ እና በ5ሺ ሜትር…
Read More
ኢትዮጵያ በፓሪስ ኦሎምፒክ የሚወክሏትን አትሌቶች መረጠች

ኢትዮጵያ በፓሪስ ኦሎምፒክ የሚወክሏትን አትሌቶች መረጠች

በየአራት ዓመቱ አንዴ የሚካሄደው የመላው ስፖርታዊ ውድድር ወይም ኦሊምፒክ የዘንድሮው ውድድር በፈረንሳይ ዋና ከተማ ፓሪስ ይካሄዳል። ውድድሩ ከሐምሌ 19 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ የሚካሄድ ሲሆን ኢትዮጵያ በውድድሩ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል ናት። በአትሌቲክስ ዘርፍ ኢትዮጵያን በውድድሩ ላይ የሚወክሉ አትሌቶች ምርጫ በስፔን ኔርሀ ትናንት ምሽት ተደርጓል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እንዳስታወቀው በ10 ሺህ ሜትር ሁለቱም ጾታ፣ በ1 ሺህ 500 ሜትር ወንዶች እንዲሁም በ800 ሜትር ወንዶች የማጣሪያ ውድድሮች ተካሂደዋል። ኢትዮጵያ ለፓሪስ ኦሎምፒክ በ10 ሺህ ሜትር ወንዶች ውድድር ለመሳተፍ የማጣሪያውን ውድድርን በትንሹ በ27 ደቂቃ ማጠናቀቅን እንደ መስፈርት አስቀምጣለች። በዚህም መሰረት በማጣሪያው ውድድር ከተሳተፉ 16 አትሌቶች ተሳትፈው ዮሚፍ ቀጄልቻ በ26፡31.01 1ኛ በሪሁ አረጋዊ 26፡31.13 2ኛ ፣ሰለሞን…
Read More